ወጣቶች
7 ስርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች የእግዚአብሔርን በረከቶች ተደራሽነትን ይጨምራሉ።


መጥምቁ ዮሐንስ ኢየሱስ ክርስቶስን ሲያጠምቅ

7.

ስርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች የእግዚአብሔርን በረከቶች ተደራሽነትን ይጨምራሉ።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 84፥20።

የሰማዩ አባታችሁ ሊያስተምራችሁና ሊባርካችሁ ይጓጓል። ይህን የሚያደርግበት አንዱ መንገድ እንደ ጥምቀት፣ ማረጋገጫ እና ቅዱስ ቁርባን ባሉ ስርዓቶች ነው። በእንደዚህ ዓይነት ስርዓቶች አማካኝነት ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን ወይም ተስፋ እንገባለን። ቃል ኪዳኖችን መጠበቅ በሕይወታችሁ ውስጥ የእግዚአብሔርን ኃይል ይጨምራል እናም ለዘላለም ሕይወት እንድትዘጋጁ ይረዳቹሃል ። ለዚህም ነው ስርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች ለእኛ ውድ የሆኑት—ምክንያቱም ከሰማይ አባታችን እና ከአዳኛችን ጋር ያለንን ግንኙነት ያጠናክራሉ እናም እነርሱን እንድንመስል ይረዱናል።

ዘለአለማዊ እውነቶች

ሥርዓቶች ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ይጠቁማሉ። ሥርዓት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያስተምር ምሳሌያዊ ትርጉም ያለው ቅዱስ ሥነ ሥርዓት ነው። ለምሳሌ ቅዱስ ቁርባን ዳቦና ውሃ ብቻ አይደለም። አዳኙን ያስታውሰናል።

ቃል ኪዳኖች የእግዚአብሔር ፍቅር፣ እምነት እና የሚጠበቁ ምልክቶች ናቸው። ከእግዚአብHሄር ጋር ያላችሁን ግንኙነት ወደ ጥልቅ ደረጃ ያደርሳሉ። ቃል ኪዳን መግባት እግዚአብሔርን እንደምትወዱ እና ለእርሱ ቁርጠኛ መሆናችሁን ያሳያል። በእርሱ ማመን ትችላላችሁ፤ እርሱም ሊያምናችሁ ይችላሉ። በዚያ ጥልቅ ቁርጠኝነት የእርሱን ኃይል የበለጠ ማግኘት እና ቃል ኪዳኖቻችሁን ስትጠብቁ እርዳታ ይመጣል።

ስትጠመቁ፣ የቤተክርስቲያን አባል መሆናቹ ሲረጋገጥ፣ ስትጸኑ እና ቅዱስ ቁርባንን ስትካፈሉ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን እየገባችሁ ነው። ስትጠመቁ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በራሳችሁ ለመውሰድ፣ እርሱን ለማገልገል እና በሕይወታችሁ በሙሉ ትእዛዛቱን ለመጠበቅ ቃል ገብታቹሃል። በቅዱስ ቁርባን ወቅት፣ እርሱን ሁል ጊዜ ለማስታወስ ቃል ገብታቹሃል። ይህ የገባችሁት ቃል ነው። እነርሱን ለመጠበቅ ፈቃደኛ ከሆናችሁ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን እንደ ቋሚ ጓደኛ እንደሚሰጣችሁ ቃል ገብቷል።

ግብዣዎች

ቅዱስ ቁርባንን እንደ ቅዱስ ስጦታ አድርጋችሁ ያዙት። በቅዱስ ቁርባን ወቅት ለቅዱስ ተሞክሮ በመዘጋጀት ለኢየሱስ ክርስቶስ ያላችሁን ቁርጠኝነት አሳዩ። ይህንን ሥርዓት የሳምንቱን መንፈሳዊ ድምቀት ለማድረግ ምን ማድረግ እንደምትችሉ አስቡ።

በሥርዓቶች ውስጥ አዳኙን ፈልጉ። አንድን ሥርዓት ስትመለከቱ ወይም ስትሳተፉ ራሳችሁን ጠይቅ፣ “ከዚህ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምን እማራለሁ?” ወይም “እንዴት ወደ እርሱ እንድቀርብ ያደርገኛል?” መንፈስ የሚያስተምራችሁን ልብ በሉ።

ቃል ኪዳኖቻችሁ ድርጊቶቻችሁን ይምሩ። ምርጫ ካላችሁ ከእግዚአብሔር ጋር ያላችሁን የቃል ኪዳን ግንኙነት አስታውሱ። ለእርሱ ታማኝ ሁኑ። እራሳችሁን ጠይቁ ይህ ከቃል ኪዳኖቼ ጋር ይጣጣማል? ለምሳሌ፣ ሌሎችን እወዳቸዋለሁ እና አገለግላቸዋለሁ፣ መጽናኛ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች አጽናናለሁ፣ እናም በሁሉም ቦታ ላይ እና ሁልጊዜም የክርስቶስ ምስክር ሆኜ እቆማለሁ?

ክርስቶስ ለኔፋውያን ቅዱስ ቁርባንን በማዘጋጀት ጠረጴዛ ላይ

ቃል የተገቡ በረከቶች

ፈተናን፣ ኃጢአትን እና የህይወት ፈተናዎችንለማሸነፍ ኃይል ሊኖራችሁ ይችላል። ቃል ኪዳኖችን መፈጸም እና መጠበቅ የእግዚአብሔርን ኃይል እንድታገኙ ያስችላቹሃል። በዚያ ኃይል ማንኛውንም ነገር በልበ ሙሉነት መጋፈጥ ትችላላችሁ። ኢየሱስ ክርስቶስ ጉልበታችሁ ነው።

ንፁህ መሆን እና ይቅር ማለት ትችላላችሁ። የጥምቀት ቃል ኪዳናችሁን እንድትጠብቁ እግዚአብሔር የገባላችሁ ቃል ኪዳን የኃጢአት ስርየት ነው። ይህ ማለት ንስሐ ስትገቡ እና ከእግዚአብሔር ጋር የገባችሁትን ቃል ስትጠብቁ እርሱ ይቅር ይላቹሃል እና እንድታሻሻሉ ይረዳቹሃል ማለት ነው።

መንፈስ ቅዱስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ሊኖር ይችላል ። ከጥምቀት እና ከቅዱስ ቁርባን ጋር የተያያዘው ሌላው የተስፋ ቃል የመንፈሱ የማያቋርጥ ጓደኝነት እና የመላእክት አገልግሎት ነው። ፈተናዎችን ብቻችሁን መጋፈጥ የለባችሁም። እግዚአብሔር የቃል ኪዳን ልጆቹን ፈጽሞ አይተወውም —በዚህ ላይ መተማመን ትችላላችሁ።

የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ሰዎች ድጋፍ ማግኘት ትችላላችሁ። በአዳኝ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የቃል ኪዳን ሰዎች ማህበረሰብ አባል ናችሁ። እርስ በርሳችሁ ታነሳላችሁ እና ትበረታታላችሁ። አብራችሁ ታዝናላችሁ፤ አብራችሁም ደስ ይላቹሃል። አንዳችሁ የሌላውን ሸክም ትሸከማላችሁ። ቤተሰብህ፣ ኤጲስ ቆጶስህ፣ መሪዎች እና ሌሎች የቤተክርስቲያን አባላት እናንተን ለመርዳት እዚህ አሉ፣ እናም እነርሱን መርዳት ትችላላችሁ።

ጥያቄዎች እና መልሶች

ያለ ሥርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች የኢየሱስ ክርስቶስ ጥሩ ተከታይ መሆን እችላለሁን? ምንም እንኳን ተጠምቀው ወይም ወደ ቤተመቅደስ ገብተው የማያውቁ ቢሆኑም ኢየሱስ ክርስቶስን ከልብ የሚከተሉ ብዙ ጥሩ ሰዎች አሉ። ይሁን እንጂ የሰማይ አባት ሁሉም ልጆቹ ፍርድዎቹን እንዲቀበሉ እና ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን እንዲገቡ ይፈልጋል ስለዚህም የእርሱን እርዳታ፣ ምህረት እና ጥንካሬ የበለጠ ማግኘት ትችላላችሁ። ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያኑን እንዲመልስ ካደረጋቸው ዋና ዋና ምክንያቶች አንዱ ይህ ነው! እያንዳንዱ የእግዚአብሔር ልጅ በዚህ ሕይወትም ሆነ በሚቀጥለው ሕይወት - ለዘለአለማዊ ሕይወት የሚያስፈልጉትን ስርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች የመቀበል እድል ይኖረዋል።

እኔ ሁል ጊዜ ለቃል ኪዳኖቼ ታማኝ አልሆንኩም ። ለእኔ ተስፋ አለ? አዎ! የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል የተስፋ እና የአዲስ ጅምር ወንጌል ነው! ለዚህም ነው በየሳምንቱ ቅዱስ ቁርባንን የምንወስደው። የሰማይ አባት ስህተት እንደምንሠራ እና አዲስ ጅማሬ እንደሚያስፈልገን ያውቅ ነበር። አዳኙ ለመመለስ መንገድ እንዲሰጥህ ህይወቱን ሰጥቷል። በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እምነት ካሳያችሁ እና ንስሐ ከገባችሁ የእግዚአብሔርን ኃይል መልሳችሁ ማግኘት ትችላላችሁ።

1ኛ ቆሮንቶስ 11፥23–26 (ቅዱስ ቁርባንን መውሰድ በኢየሱስ ክርስቶስ እና በስርየቱ እንደምናምን ያሳያል)፤ ሞዛያ 18፥10፣ 13 (የጥምቀት ቃል ኪዳን)፤ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 13 (የአሮናዊ ክህነት የንስሐ፣ የጥምቀት እና የመላእክትን አገልግሎት ቁልፎችን ያጠቃልላል)፤ 20፥37 (ለጥምቀት መስፈርቶች)፤ 20፥77፣ 79 (የቅዱስ ቁርባን ጸሎቶች) ተመልከቱ።

የቤተመቅደስ መግቢያ መታወቂያ ለማግኘት የሚጠየቅ ጥያቄ

  • የሰንበትን ቀን በቤትም ሆነ በቤተክርስቲያን ቅዱስ አድርጎ ለመጠበቅ፤ በስብስባዎች ለመገኘት፤ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ለመዘጋጀት እና በብቁነት ለመውሰድ፤ እንዲሁም ህይወትህን/ህይወትሽን ከወንጌል ህግጋት እና ትዕዛዛት ጋር አስማምተህ/ሽ ለመኖር ትጥራለህ/ትጥሪያለሽ?