“ጥቅምት 26–ህዳር 1 “ልቅሶአቸውንም ወደ ደስታ እመልሳለሁ”፦ ኤርምያስ 31፥33፤ 36፥39 ሰቆቃው ኤርምያስ 1፥3” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ) [2026 (እ.አ.አ)]
“ጥቅምት 26–ህዳር 1 “ልቅሶአቸውንም ወደ ደስታ እመልሳለሁ፣” ኑ፣ ተከተሉኝ፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ)
ኤርሚያስ ስለኢየሩሳሌም መጥፋት እያለቀሰ፣፣ በሬምብራንድት ቫን ሪጅን
ጥቅምት 26–ህዳር 1፤ “ልቅሶአቸውንም ወደ ደስታ እመልሳለሁ”
ኤርምያስ 31–33፤ 36–39፤ ሰቆቃው ኤርምያስ 1፤ 3
እግዚአብሔር መጀመሪያ ኤርምያስን ነብይ እንዲሆን ሲጠራው የእሱ ተልዕኮ “[መንቀል] እና [ማፍረስ]” እንደሆነ ነገረው (ኤርምያስ 1፥10)—እናም በኢየሩሳሌም ውስጥ ብዙ የሚነቀሉ እና የሚፈርሱ ክፋቶች ነበሩ። ነገር ግን ያ የኤርምያስ ተልዕኮ አንዱ ክፍል ብቻ ነበር—እንዲሁም “[ሊ]ሰራ እና [ሊ]ተክል” ተጠርቶም ነበር (ኤርምያስ 1፥10)። የቃል ኪዳኑ ሕዝብ አመፅ በቀረው ባድማ ውስጥ ምን ሊገነባ ወይም ሊተከል ይችላል? በሌላ መንገድ ስንጠየቅ፣ ኃጢአት ወይም መከራ ሕይወታችንን ሲያፈራርስ፣ እንደገና መገንባትና መትከል የምንችለው እንዴት ነው? መልሱ ያለው “የጽድቅ ቁጥቋጥ” (ኤርምያስ 33፥15)፣ በሆነው ቃል በተገባው መሲህ ላይ ነው። “አዲስ ቃልኪዳን” ያመጣል (ኤርምያስ 31፥31)—ከውጫዊ የአምልኮት ገጽታ የበለጠ ይጠይቃል። የእርሱ ህግ “በውስጣችን” “በልቦቻችን” የተፃፈ መሆን አለበት። ያ ነው እግዚአብሔር “[የእኛ] አምላክ” እና እኛ ደግሞ “[የእርሱ] ህዝብ ነን” ማለት (ኤርምያስ 31፥33)። የእድሜ ልክ ሂደት ነው፣ እንዲሁም ስህተቶችን እንሰራለን እናም ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚያስለቅስ ምክንያት ይገጥመናል። ነገር ግን እኛ ስናደርግ፣ ጌታ ቃል ገብቷል፦ “ልቅሶአቸውንም ወደ ደስታ እመልሳለሁ” (ኤርምያስ 31፥13)።
የሰቆቃወ ኤርምያስን አጠቃላይ እይታ ለማግኘት በቅዱሳን ጽሑፎች መመሪያ ውስጥ የሚገኘውን “ሰቆቃወ ኤርምያስ፣ መጽሐፍ” የሚለውን ተመልከቱ።
በቤት እና በቤተክርስቲያን ለመማር የሚረዱ ሃሳቦች
ኤርምያስ 31፤ 33
ጌታ የቃል ኪዳኑን ህዝብ ከምርኮ ያወጣል።
በ ኤርምያስ 31፤ 33 ውስጥ እስራኤላውያን ወደ ምርኮ ውስጥ ሲገቡ ስለሚያጋጠማቸው “ዋይታ እና የመራራ ለቅሶ” ጌታ እውቅና ሰጠ (ኤርምያስ 31፥15)። ይሁን እንጂ፣ የመፅናናት እና የተስፋ ቃላትንም ሰጣቸው። እነዚህን ምዕራፎች ስታነቡ ፈልጋቸው። እናንተን የሚመለከቱ ምን ተስፋዎች አግኝታችኋልል?
ኤርምያስ 31፥31–34፤ 32፥37–42
“እነርሱም ህዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ።”
እስራኤላውያን ከጌታ ጋር የነበራቸውን ቃልኪዳን ቢያፈርሱም እንኳን፣ እግዚአብሔር ከህዝቡ ጋር በድጋሚ “አዲስ” እና “የዘላለም ቃልኪዳን” እንደሚመሰርት ኤርምያስ ተነበየ (ኤርምያስ 31፥31፤ 32፥40)። ያ ቃል ኪዳን ምንድን ነው? በቅዱሣት መፃህፍት መመሪያ ውስጥ፣ “New and Everlasting Covenant [አዲስ እና የዘላለም ቃል ኪዳን]፣” በወንጌል ቤተመጻህፍት ተመልከቱ።
ስታነብ፡-ኤርምያስ 31፥31–34፤ 32፥37–42፣ አስላስሉ
-
የእግዚአብሔር የቃል ኪዳን ሕዝብ አካል መሆን ለእናንተ ምን ማለት ነው።
-
የእርሱን ህግ በልቦ ውስጥ መፃፍ ማለት ምን ማለት ነው።
-
ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን ስትገቡ ጌታ የገባውን ቃል ምንድ ነው።
-
ከጌታ ጋር ያላችሁ የቃል ኪዳን ግንኙነት እንዴት የሚለወጠው።
በቅዱስ ስነስርዓቶች ውስጥ ስትሳተፉ ለእግዚአብሔር ምን ቃል ገብተቹሃል? እነዚያን ቃል ኪዳኖች የፈፀመው እንዴት ነው?
በተጨማሪም ዴቪድ ኤ. ቤድናርን፣ “Abide in Me, and I in You; Therefore Walk with Me [በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ፤ ስለዚህ ከእኔ ጋር ተራመዱ]፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2023 (እ.አ.አ)፣ 123-26 ተመልከቱ።
ኤርምያስ 36
ቅዱሳን መጽሐፍት እኔን ከክፉ ለማሸሽ ኃይል አላቸው።
በኤርምያስ 36፥2-3 መሰረት እግዚአብሔር ኤርምያስን ትንቢቶቹን እንዲጽፍ ያዘዘው ለምንድን ነው? ኤርምያስ 36ን ስታነቡ የሚከተሉት ሰዎች ስለእነዚህ ትንቢቶች እንዴት እንደተሰማቸው መመዝገብን አስቡ፦
-
ጌታ (ቁጥሮች 1–3፣ 27–31ተመልከቱ)
-
ኤርምያስ (ቁጥር 4–7፣ 32 ተመልከቱ)።
-
ባሮክ (ቁጥር 4፥8–10፣ 14–18 ተመልከቱ።)
-
ይሁዲ እና ንጉሥ ኢዮአቄም (ቁጥር 20-26 ተመልከቱ)
-
ኤልናታን፣ ድላያ እና ገማርያ (ቁጥር 25ተመልከቱ)
ስለ ቅዱሳን ጽሑፎች ምን እንደሚሰማችሁ አስቡ። ከክፉ እንዲሸሹ እንዴት ረድቶዎት ያውቃሉ?
ኤርምያስ 37–39
የእግዚአብሔርን ነቢያት በመከተል ፅኑ።
በኤርምያስ 37፥1–3፤ 15–21፤ 38፥1–6፤ 14–28፣ ንጉሥ ሴዴቅያስ ኤርምያስ የጌታ እውነተኛ ነቢይ መሆኑን እንዳመነ ምን ማስረጃ ታያላችሁ? ሴዴቅያስ ያላመነበትን ምን ማስረጃ ታያላችሁ? ከዚህ ንጽጽር ምን ተማራችሁ? ኤርምያስ 39ን በምታነብበት ጊዜ ሴዴቅያስ እና ህዝቡ ነቢዩን ቢከተሉ እና የጌታን ትእዛዛት ቢጠብቁ ልዩነቱን አስቡ። (በሴዴቅያስ ላይ የደረሰውን በ1 ኔፊ 1፥2 በሌሂ ቤተሰብ ላይ ከደረሰው ጋር አወዳድሩ።)
ኤርምያስ 38፥6–13፤ 39፥15–18
ለትክክለኛው ነገር በድፍረት መቆም እችላለሁ።
የንጉሡ ባለ ሥልጣናት የኤርምያስ ትንቢት ወታደሮቻቸውን ለመዋጋት ፈቃደኛ እንዳይሆኑ እንዳደረጋቸው ስላሰቡ ኤርምያስን ቆሻሻ ጉድጓድ ውስጥ ጣሉት (ኤርምያስ 38፥1–4ተመልከቱ)። በኤርምያስ 38፥6–13፣ ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ የሰጠው ምላሽ ምን አስደነቃችሁ? በትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 39፥15-18ላይ ጌታ ለአቤሜሌክ የሰጠውን በረከትም አስተውሉ።
የአቤሜሌክን ምሳሌ መከተል የምትችሉት እንዴት ነው?
የኤርምያስ ለቅሶ
ሰቆቃው ኤርምያስ 1፤ 3
በኃጢአት ምክንያት ያጋጠመኝን ሀዘን ጌታ ሊያቃልልልኝ ይችላል።
የሰቆቃው ኤርምያስ መጽሐፍ ከኢየሩሳሌም እና ከቤተመቅደሷ ውድመት በኋላ የተፃፉ ግጥሞች ስብስብ ነው። መቋቋማቸው አስፈላጊ የሆነው ለምን ይመስላችኋል? በ ሰቆቃው ኤርምያስ1 እና3 ውስጥ የትኛው ምሳሌያዊ አነጋገር እስራኤላውያን የተሰማቸውን ታላቅ ሃዘን ለመገንዘብ እንደረዳችሁ አስቡ። ምን የክርስቶስ የተስፋ መልዕክቶችን ታገኛላችሁ? (በተለይ ሰቆቃው ኤርምያስ 3፥20–33፤ እንዲሁም ማቴዎስ 5፥4፤ ያዕቆብ 4፥8–10፤ አልማ 36፥17–20ተመልከቱ)።
ፕሬዘደንት ኤም ራስል ባላርድ አንዳንዶች ተስፋ እንዲቆርጡ የሚያደርጉ በርካታ ሁኔታዎችን ጠቅሰዋል፣ እና የት ተስፋ ማግኘት እንደሚችሉ ምክር ሰጥተዋል፡-
“አንዳንዶቻችን ህይወታችን በጭንቀት፣ በብስጭት እና በሀዘን የተሞላ ሆኖ ልናገኘው እንችላለን። ብዙዎች በዓለም ላይ ተስፋፍቶ የሚመስለውን ትርምስ ለመቋቋም አቅመ ቢስ እንደሆኑ ይሰማቸዋል። ሌሎች ደግሞ እየተዳከሙ ባሉ የቤተሰባቸው አባላት በፍጥነት እየተሸፈኑ ባሉ የቤተሰባቸው አባላት ይጨነቃሉ። ብዙዎች የዓለምን ክፋትና ጭካኔ የማይጠገን አድርገው ለመቀበል ራሳቸውን አቁመዋል። ተስፋ ቆርጠዋል።
“… ከመካከላችን አንዳንዶቹ በኃጢያት እና በመተላለፍ ምክንያት ሙሉ ተስፋ አጥተው ይሆናል። አንድ ሰው በዓለም መንገዶች ውስጥ በጣም ከመጠመዱ የተነሳ መውጫውን አያይም እና ሙሉ በሙሉ ተስፋ ይቆርጣል። በዚህ የጠላት ወጥመድ ውስጥ ለወደቁ ሁሉ የምለምነው ተስፋ እንዳትቆርጡ ነው! ነገሮች ምንም ያህል ተስፋ የቆረጡ ቢመስሉም ወይም ተስፋ ቢስ ቢሆኑም፣ እባካችሁ እመኑኝ፣ ሁልጊዜም ተስፋ ሊኖራችሁ ይችላል። ሁሌም” (“The Joy of Hope Fulfilled [የተስፋ ደስታ ተፈጸመ]፣” ኢንዛይን፣ ሀዳር 1992 (እ.አ.አ) 31-32)።
በተጨማሪም “Come, Ye Disconsolate,” መዝሙር፣ ቁጥር. 115።
ሌሎች ለራሳቸው ትምህርት ሃላፊነት እንዲወስዱ እርዷቸው። አንዳንድ ጊዜ ለማስተማር ቀላሉ መንገድ ተማሪዎች ማወቅ አለባቸው ብለን የምናስበውን ብቻ መንገር ይመስላል። ይሁን እንጂ ቀላሉ መንገድ ሁልጊዜ የተሻለው መንገድ አይደለም። ሽማግሌ ዴቪድ ኤ. ቤድናር አስተምሯል፡- “ዓላማችን ‘ምን ልነግራቸው?” መሆን የለበትም። ከዚያ ይልቅ፣ እራሳችንን መጠየቅ ያለብን የሚከተሉትን ጥያቄዎች ነው፣ ‘ምን እንዲያደርጉ ልጋብዛቸው? ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኞች ከሆኑ መንፈስ ቅዱስን ወደ ሕይወታቸው መጋበዝ የሚጀምሩት ምን አይነት አነሳሽ ጥያቄዎችን ልንጠይቃቸው እንችላለን?’” (evening with a General Authority [ምሽት ከአጠቃላይ አመራሮች ጋር]፣ የካቲት 7፣ 2020 (እ.አ.አ)፣ broadcasts.ChurchofJesusChrist.org እንዲሁም Teaching in the Savior’s Way[በአዳኝ መንገድ ማስተማር]፣ 25ተመልከቱ)። ተማሪዎች ለትምህርታቸው ሃላፊነት እንዲወስዱ ለመርዳት ብዙ መንገዶች አሉ። ለምሳሌ፣ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ተማሪዎች እንዲፈልጉ፣ እንዲያስቡ፣ ዝርዝሮችን እንዲሰሩ፣ ስዕሎችን እንዲመለከቱ፣ በነገር ትምህርቶች እንዲሳተፉ፣ እንዲስሉ እና እንዲያካፍሉ እና የተማሩትን እንዲተገብሩ ተጋብዘዋል።
ልጆችን ለማስተማር የሚረዱ ሀሳቦች
ኤርምያስ 31፥3
የሰማይ አባት እና ኢየሱስ “በዘላለም ፍቅር” ይወዱኛል።
-
ኤርምያስ 31፥3ን ከልጆቻችሁ ጋር ስታነቡ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ነገሮችን (ወይም የዕቃዎችን ሥዕሎች) ለምሳሌ እንደ ብረት ሳንቲም እና አንዳንድ እንደ ቁራጭ ፍሬ ያሉ ነገሮችን እንድታገኙ ሊረዱሃችሁ ይችላሉ። “ዘላለማዊ” ማለት ምን ማለት እንደሆነ መነጋገር እና የሰማይ አባት “የዘላለም ፍቅር” እንዴት እንደተሰማችሁ አንዳችሁ ለሌላችሁ ማካፈል ትችላላችሁ። “God Is Watching Over All [እግዚአብሔር ሁሉን ይመለከታል]፣” የሚለውን መዝሙር ልትዘምሩም ትችላላችሁ (የልጆች መዝሙር መጽሃፍ፣229)።
ኤርምያስ 31፥31–34፤ 32፥38–41
እግዚአብሔር ቃል ኪዳኔን እንድጠብቅ ይረዳኛል።
-
ልጆቻችሁ ልብን በወረቀት ላይ መሳል እና ከኤርምያስ 31፥31–34 ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን ስለመግባት የተማሯቸውን ነገሮች በልቡ ውስጥ መጻፍ ያስደስታቸው ይሆናል። በጥምቀት ጊዜ የገቡትን ቃል ኪዳን መከለስ (ሞዛያ 18፥10፣ 13ተመልከቱ) እና እነዚህን ተስፋዎች በልባቸው መፃፍ ምን ማለት እንደሆነ መወያየት ትፈልጉ ይሆናል።
ኤርምያስ 36፥1–4።
ቅዱሳት መጻህፍት የእግዚአብሔር ቃል ናቸው።
-
የዚህ ሳምንት የአክቲቪቲ ገጽ ልጆቻችሁ ስለ ኤርምያስ፣ ባሮክ እና ንጉሡ እንዲያውቁ ሊረዳቸው ይችላል (ኤርምያስ 36ተመልከቱ)። እንዲሁም በኤርምያስ 36፥4-10፣ ውስጥ ካሉት ቃላቶች ጋር አብረው የሚሄዱ ድርጊቶችን ሊያደርጉ ይችላሉ፣ ለምሳሌ በመፅሃፍ ውስጥ መጻፍ (ቁጥር 4ተመልከቱ) እና ቅዱሳት መጻህፍትን ለሰዎች ማንበብ (ቁጥር 8፣10ተመልከቱ)።
-
እናንተ እና ልጆቻችሁ የልጆችን መጽሐፍ እና የቅዱሳት መጻህፍት ግልባጭ በመመልከት እነዚህ መጻሕፍት እንዴት እንደሚለያዩ ማውራት ትችላላችሁ። ቅዱሳት መጻሕፍትን ልዩ የሚያደርጋቸው ምንድን ነው? ለእናንተ ልዩ የሆኑ አንዳንድ የቅዱሣት መፃህፍት ምንባቦችን አንዳችን ለሌላችን መካፈላችን የሚያነሣሣ ሊሆን ይችላል።
ኤርምያስ 38፥6-13
ለትክክለኛው ነገር መቆም እችላለሁ
-
ልጆቻችሁ የአቤሜሌክን ታሪክ በዓይነ ሕሊናህ እንዲመለከቱ ለመርዳት በመግቢያው መጨረሻ ላይ ያለውን ሥዕል ልትጠቀሙ ትችላላችሁ በኤርምያስ 38፥6-13። ምናልባት አቤሜሌክ የጌታን ነቢይ ለመርዳት ደፋር ነገር ያደረገበትን ጥቅስ እንዲያገኙ ልትረዷቸው ትችላላችሁ። ዛሬ ነብያችን በእግዚአብሔር እንደተጠሩ ማወቃችንን ለማሳየት ምን እናድርግ?
ሰቆቃወ ኤርምያስ 1፥1–2፣ 16፤ 3፥22-26
አዳኙ ኃጢአቴ ይቅር እንዲባልልኝ አስችሏል።
-
ሰቆቃወ ኤርምያስን ለማስተዋወቅ፣ እስራኤላውያን ንስሐ ስላልገቡ ኢየሩሳሌምና ቤተ መቅደሱ እንደወደሙ ለልጆቻችሁ ማስረዳት ትፈልጉ ይሆናል። በዚያን ጊዜ የምትኖሩ ከሆነ ምን ሊሰማችሁ እንደሚችል እርስ በርሳችሁ ልታካፍሉ ትችላላችሁ (ሰቆቃወ ኤርምያስ 1፥1–2፣ 16ተመልከቱ)። በ ሰቆቃወ ኤርምያስ 3፥22-26 ላይ ያለው መልእክት ተስፋ የሰጣችሁ እንዴት ሊሆን ይችላል?
-
እንዲሁም በመረጣችሁት መጥፎ ምርጫ ምክንያት ስላዘናችሁበት ጊዜ እርስ በርሳችሁ መነጋገር ትችላላችሁ። ሰቆቃወ ኤርምያስ 3፥22-26 ኢየሱስ ክርስቶስ የሚሰጠውን ይቅርታ እንድንረዳ የሚረዳን ምን እናገኛለን?
ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የጓደኛ መጽሔት ዕትም ተመልከቱ።