“ህዳር 2–8 (እ.አ.አ)። “አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ”፦ ሕዝቅኤል 1፥3፤ 33፥34፤ 36፥37፤ 47፣” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ) [2026 (እ.አ.አ)]
“ህዳር 2–8 (እ.አ.አ)። “አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ”፦ ኑ፣ ተከተሉኝ፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ)
ህዳር 2–8 (እ.አ.አ) “አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ”
ሕዝቅኤል 1፥3፤ 33፥34፤ 36፥37፤ 47
ሕዝቅኤል በስደት የነበረ ነብይ ነበር። ከሌሎች እስራኤላውያን ጋር ተይዞ ወደ ባቢሎን ለግዞት ተልኮ ነበር። በኢየሩሳሌም ውስጥ ሕዝቅኤል በቤተመቅደስ ውስጥ እንደ ካህን ሆኖ ያገለግል ነበር። በባቢሎን ውስጥ እሱ በምርኮ ከተወሰዱት መካከል አንዱ ነበር እና በተቀመጡበት ተቀምጧል (ሕዝቅኤል 3፥15) ከተወደደው የእግዚአብሔር ቤት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮች ርቆ የነበረው እና የመመለስ ተስፋ አልነበረውም። ከዚያም አንድ ቀን ሕዝቅኤል ህልምን አየ። “የእግዚአበሔር ክብር[ን]” አየ (ሕዝቅኤል 1፥28)—በኢየሩሳሌም ባለው ቤተመቅደስ ውስጥ ሳይሆን ነገር ግን እዛው በባቢሎን በስደት ውስጥ እያለ። በኢየሩሳሌም ያለው ክፋት የእግዚአብሔር መገኘት እዛ እስከማይኖር ድረስ እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ ተማረ ( ሕዝቅኤል 8–11፤ 33፥21ይመልከቱ)።
ሆኖም በሕዝቅኤል መልእክት ውስጥ አንድ ተስፋ ያለው ነገር አለ። የቃል ኪዳኑ ሰዎች የቱን ያህል የወደቁ ቢሆንም፣ እግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ አልተዋቸውም። “የእግዚአብሔርን ቃል [ለመስማት]” ቢፈልጉ (ሕዝቅኤል 37፥4)፣ ጥሪውን ቢቀበሉ ሞቶ የነበረ ነገር መልሶ ሕይወት ይዘራል። “የድንጋዩ ልብ” በ “[በስጋ] ልብ” ሊተካ ይችላል (ሕዝቅኤል 36፥26)። በመጨረሻ ቀናትም፣ እግዚአብሔር አዲስ ቤተመቅደስን እና አዲስ ኢየሩሳሌምን ይመሰርታል “ከዚያም ቀን ጀምሮ የከተማይቱ ስም እግዚአብሔር በዚያ አለ ተብሎ ይጠራል” (ሕዝቅኤል 48፥35)።
ለሕዝቅኤል መጽሐፍ አጠቃላይ እይታ፣ “ሕዝቅኤል ” በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ውስጥ ተመልከቱ።
በቤት እና በቤተክርስቲያን ለመማር የሚረዱ ሃሳቦች
ሕዝቅኤል 3፤ 34
ጌታ በጎቹን እንድመግብ ጋብዞኛል።
በ ሕዝቅኤል34 እና 34፣ ጌታ የህዝቡን መሪዎች እንደ ጠባቂ እና እረኛ አድርጎ ይጠቅሳል። እነዚህን ምዕራፎች ስታነቡ፣ መሪ መሆን ምን ማለት እንደሆነ እነዚህ ርዕሶች ምን እንደሚጠቁሙ አስቡ።
እግዚአብሔር እንድትመግቧቸው የሚፈልገው “በጎች” እነማን ናቸው? አንድ ሰው ተልእኮ ለማገልገል፣ ልጆችን ለማሳደግ፣ ወይም የአገልግሎቱን ተልዕኮ ለመፈጸም የሚረዳውን በ ሕዝቅኤል 34 ላይ ምን ታገኛላችሁ? እንደ እረኛችን የአዳኝን ምሳሌ መከተል የምትችለው እንዴት ነው? ( ቁጥሮች 11–31ን ተመልከቱ)።
እንዲሁም በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ያገኙትን ምሳሌያዊነት ማሰላሰል ትችላላችሁ። በቁጥር 14 ላይ “መልካሙ የግጦሽ መስክ” እና “ጥሩ በረት” ምን ሊወክሉ ይችላሉ? በግ “በጠፋ” እና “በተባረረው” መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው? (ቁጥር 16)። ምን ሌሎች ምልክቶችን ታያላችሁ?
በተጨማሪ ዮሃንስ 21፥ 15-17፤ ጌሪት ደብሊው ጎንግ፣ “Ministering [ማገልገል]፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2023 (እ.አ.አ)፣ 16-19 ተመልከቱ።
ሕዝቅኤል 33፥10–19
ጌታ ይቅር ለማለት ይፈልጋል።
የተማረኩ እስራኤላውያን ፣ “ሃጢያታችን በላያችን [ካ]ሉ”፣ “እንዴትስ በሕይወት እንኖራለን?” ሲሉ ተደነቁ (ሕዝቅኤል 33፥10)። በምላሹም ጌታ ስለ ንስሐና ስለ ይቅርታ አስተማራቸው። እነዚህ ጥያቄዎች እሱ ያስተማረውን እንድታሰላስሉ ሊረዷችሁ ይችላሉ፡-
-
“[በገዛ ጽድቅ መታመን]” ማለት ምን ማለት ይመስላቹሃል? ( ሕዝቅኤል 33፥12–13ተመልከቱ)።
-
በ ሕዝቅኤል 33፥12–19 ውስጥ የተገለፁት ሰዎች ፍትሃዊ እንዳልሆኑ ለሚሰማው ሰው ምን ትላላችሁ? ( ማቴዎስ 21፥28–31፤ ሉቃስ 18፥9–14ተመልከቱ)።
-
በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ንስሐ መግባት ማለት ምን ማለት እንደሆነ ለመረዳት የሚረዳችሁ ምንድን ነው? በ ሕዝቅኤል 36፥26–27 እና አልማ 7፥14–16፣ ውስጥ ምን ተጨማሪ ግንዛቤዎችን ታገኛላችሁ?
ሕዝቅኤል 37
እግዚአብሔር ህዝቦቹን እየሰበሰበ እና አዲስ ሕይወት እየሰጠ ነው።
የእስራኤል መሰብሰብ በ ሕዝቅኤል37 ውስጥ በሁለት ምልክቶች ተገልጿል። ስለ መጀመሪያው—የሞቱ አጥንቶች ወደ ሕይወት ስለመመሳቸው ስታነቡ ( ቁጥሮች 1–14ተመልከቱ)— በመጋረጃው በሁለቱም በኩል ያሉትን እስራኤልን ስለመሰብሰብ ምን እንደተማራችሁ አሰላስሉ( ሕዝቅኤል 36፥24–30ተመልከቱ)። እነዚህን የመሳሰሉ ጥያቄዎችን አስቡባቸው፡-
-
ጌታ ስለእስራኤል መሰብሰብ ምን ለማድረግ እየሞከረ ነው?
-
እንዴት እያከናወነው ነው?
ስለ ሁለተኛው ምልክት ከ ቁጥር 15-28 ስታነቡ እነዚህን ተመሳሳይ ጥያቄዎች ራሳችሁን መጠየቅ ትችላላችሁ። ይህ ምልክት ሁለት እንጨቶችን ያካትታል፣ ብዙ ሊቃውንት በእንጥልጥል የተገጣጠሙ የእንጨት መፃፊያ ሰሌዳዎች ብለው ይተረጉማሉ የይሁዳ በትር መጽሐፍ ቅዱስን ሊወክል ይችላል (የመጽሐፍ ቅዱስ የበለጠው ድርሻ ያለው በይሁዳ ዘሮች ስለተፃፈ) እንዲሁም የዮሴፍ በትር መጽሐፈ ሞርሞንን ሊወክል ይችላል (የሌሂ ቤተሰቦች የግብፁ ዮሴፍ ዘሮች ስሆኑ)። ያንን በአዕምሮ ውስጥ በመያዝ እነዚህ ጥቅሶች እስራኤላውያንን በመሰብሰብ ረገድ ስለቅዱሳን መጻህፍት ድርሻ ምን አስተማሮት?
መጽሐፍ ቅዱስ እና መፅሐፈ ሞርሞን በህይወታችሁ ውስጥ እንዴት አብረው እንደሰሩ አስቡ—በተለይም ወደ ክርስቶስ እንድትመጡ ለመርዳት። በተለይ ለእናንተ ትርጉም ያላቸው ምን ምን ክፍሎች ነበሩ?
እንዲሁም2 ኔፊ 3፥11–13፤ 29:14፤ “Israel, Israel, God Is Calling [እስራኤል፣ እስራኤል፣ እግዚአብሔር እየጠራ ነው]፣” መዝሙር፣ ቁጥር 7 ርዕሶች እና ጥያቄዎች፣ “Bible [መጽሐፍ ቅዱስ]፣” “Book of Mormon [መጽሐፈ ሞርሞን]፣” የወንጌል ቤተ መጻሕፍት፤ “The Book of Mormon Gathers Scattered Israel” (ቪዲዮ)፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ተመልከቱ።
The Book of Mormon Gathers Scattered Israel
ሕዝቅኤል በራዕይ ላይ ወንዝ ከቤተ መቅደሱ ሲፈስና የሙት ባሕርን ሲፈውስ አይቷል።
ሕዝቅኤል 47፥1–12
በጌታ ቤት ውስጥ መንፈሳዊ ፈውስ ማግኘት እችላለሁ።
ሕዝቅኤል 47፥1–12 ን ስታነብ፣ የሙት ባሕር በጣም ጨዋማ በመሆኑ ዓሦችና ዕፅዋት ሊኖሩበት እንደማይችሉ ማወቁ ሊጠቅም ይችላል። በቁጥር 1-12 ላይ ስለተገለጸው ውሃ ምን ያስደንቃችኋል? (እንዲሁም ራእይ 22፥1ተመልከት)። እነዚህ ውኃዎች ምን ሊያመለክቱ ይችላሉ? በቁጥር 12 ላይ የተገለጹት ዛፎች ምንን ሊያመለክቱ ይችላሉ?
“Family History and Temple Work: Sealing and Healing [የቤተሰብ ታሪክ እና የቤተመቅደስ ስራ፦ መታተም እና መፈወስ]” የሚለው የሽማግሌ ዴል ጂ. ረንለንድ መልዕክት ምን ግንዛቤ ይጨምርላችኋል? (ሊያሆና፣ ግንቦት 2018፣ 47–48 ተመልከቱ)። በቤተመቅደስ ምክንያት መንፈሳዊ ህይወት እና ፈውስ እንዴት እንዳገኛችሁ አሰላስሉ።
ልጆችን ለማስተማር የሚረዱ ሀሳቦች
ሕዝቅኤል 3፥17፤ 33፥1–5
ነቢያት ስለ አደጋ እንደሚያስጠነቅቁን ጠባቂዎች ናቸው።
-
ትንንሽ ልጆች ከሕዝቅኤል 3፥17 ጋር የሚስማሙ ድርጊቶችን ሲፈጽሙ ያስደስታቸው ይሆናል። ለምሳሌ “ጠባቂ”፣ “ሰሚ” እና “አፍ” የሚሉትን ቃላት ስታነብ ወደ ዓይኖቻቸው፣ ወደ ጆሮአቸው እና ወደ አፋቸው ሊያመለክቱ ይችላሉ። ከቤት ውጭ ወይም በክፍሉ ዙሪያ የእግር ጉዞ ማድረግን ሊወዱ ይችላሉ። ሲራመዱ፣ በመንገዱ ላይ ስላሉት ነገሮች፣ እንደ ወንዞች ለመዝለል፣ ስለ ዳክዬ ቅርንጫፎች፣ ወይም ስለ እንስሳት (እውነተኛ ወይም ማስመሰል) አስጠነቅቋቸው። ይህ የጌታ ነቢይ ማየት የማንችላቸውን አደጋዎች እንዴት እንደሚያስጠነቅቀን ወደ ውይይት ሊያመራ ይችላል።
-
ለማብራራት ሌላ መንገድ ይኸውና ሕዝቅኤል 3፥17፤ 33፥1–5። ከልጆችዎ አንዱ በመስኮት በመመልከት እና ውጭ የሆነውን ሁሉ በመንገር “ጠባቂ” መስሎ ሊቀርብ ይችላል። እንዲሁም “Watchman on the Tower [በግንብ ላይ ጠባቂ]” የሚለውን ቪዲዮ ማየት ትችላለህ (ChurchofJesusChrist.org). በሕይወት ያለው ነብያችን እንዴት ነው ለእኛ እንደመለከት ነፊ የሆነው?
4:17Watchman on the Tower
ነቢዩ ሕዝቅኤል፣ በላይል ቤዴስ
ሕዝቅኤል 37፥15–23
መጽሐፍ ቅዱስ እና መፅሐፈ ሞርሞን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ “እንዲሰበስቡ” ረድተውናል።
-
ሕዝቅኤል 37፥15–23ን አንድ ላይ ካነበባችሁ በኋላ፣ እናንተ እና ልጆቻችሁ ሁለት እንጨቶችን ፈልጋችሁ በአንዱ ላይ ለይሁዳ (መጽሐፍ ቅዱስ) እና በሌላው ላይ ለዮሴፍ (መጽሐፈ ሞርሞን) ጻፉ። ከዚያም ወደ አዳኙ እንዲቀርቡ እና “[የእርሱ] ህዝብ” እንዲሆኑ የሚረዷቸውን ታሪኮች ወይም ጥቅሶች ከመጽሐፍ ቅዱስ እና ከመጽሐፈ ሞርሞን ሊታካፍሉ ትችላላችሁ (ቁጥር23)። እነዚህን ሁለት የቅዱሳት መጻሕፍት ማግኘት ለምን ጥሩ ነው?
ሁሉንም ነገር ለመሸፈን አትሞክሩ። በሕዝቅኤል ያለውን እውነት ሁሉ ከልጆቻችሁ ጋር መመርመር አትችሉ ይሆናል። መረዳት ያለባቸውን ነገር በጸሎት ምእንፈስ አስቡ እንዲሁም በምን ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ለመወሰን መንፈሳዊ መመሪያን ፈልጉ። (Teaching in the Savior’s Way [በአዳኙ መንገድ ማስተማር]፣ 17ን ተመልከቱ።)
ሕዝቅኤል 47፥1–12
ልባችን እና ቤተሰቦቻችን በጌታ ቤት ውስጥ ፈውስ ማግኘት ይችላሉ።
-
ሕዝቅኤል 47 ሕዝቅኤል ከቤተ መቅደሱ የሚፈሰውን ውኃና የሙት ባሕርን እንደሚፈውስ የተመለከተውን ራእይ ይገልፃል። ምናልባት ልጆቻችሁ እያንዳንዳቸው እንደ ቤተመቅደስ፣ ወንዝ፣ በረሃ፣ ሙት ባህር፣ ብዙ ዓሳ ወይም ፍሬያማ ዛፍ ካሉ ራእዩ አንድ ወይም ሁለት ነገሮችን ይሳሉ። ከዚያም፣ ከቁጥር1–12 ያሉትን አንድ ላይ ስታነቡ፣ ያ ነገር ሲጠቀስ ስዕላቸውን ሊጋሩ ይችላሉ። በዚህ ራእይ ውስጥ ከወንዙ ምን በረከቶች መጡ? ልጆቹ እነዚህ በረከቶች እንዴት የቤተመቅደስ ቃል ኪዳኖችን ለሚያከብሩ አዳኝ የሚያቀርባቸውን በረከቶች እንዲያዩ እርዷቸው። “And the River Will Grow [ወንዙም ይበቅላል]” (የወንጌል ቤተ መጻሕፍት) የሚለው ቪዲዮ ሊረዳ ይችላል።
3:43And the River Will Grow
-
እንዲሁም የቤተመቅደስን በረከቶች የሚገልጽ መዝሙር አብራችሁ፣ ለምሳሌ “Families Can Be Together Forever [ቤተሰቦች ለዘላለም አብረው ሊሆኑ ይችላሉ]” (የልጆች የመዝሙር መጽሐፍ፣ 188) መዘመርም ትችላላችሁ። ጌታ በቅዱስ ቤቱ እንዴት እንደሚባርከን ይህ መዝሙር ምን ያስተምረናል?
ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የጓደኛ መጽሔት ዕትም ተመልከቱ።