“መስከረም 21-27 (እ.አ.አ)። ‘ድንቅ ነገርን እና ተአምራትን’፦ ኢሳይያስ 13-14፤ 22፤ 24-30፤ 35፣” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ) (2026 እ.አ.አ)
“መስከረም 21-27 (እ.አ.አ)። ‘ድንቅ ነገርን እና ተአምራትን፣’” ኑ፣ ተከተሉኝ፦ 2026(እ.አ.አ)
ቅዱስ ጫካ፣ በብሬንት ቦረፕ
መስከረም 21-27፦ “ድንቅ ነገርን እና ተአምራትን”
ኢሳይያስ 13–14፤ 22፤ 24–30፤ 35
እግዚአብሔር ነብያቶችን እንዲያደርጉ ከጠየቃቸው ነገሮች አንዱ ስለሃጢያት ውጤቶች እንዲያስጠነቅቁ ነው። በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ ነቢያት፣ ኃያላን የነበሩ መንግሥታት ገዢዎች ንስሐ መግባት እንዳለባቸው ይነግሯቸው ነበር። አደገኛ ስራ ነበር ነገር ግን ኢሳይያስ አልፈራም ነበር እናም—ለእስራኤል፣ ለይሁዳ እና በዙሪያው ላሉ አገራት ጨምሮ—በእሱ ዘመን ለነበሩት መንግሥታት ማስጠንቀቂያው ደፋር ነበር ( ኢሳይያስ 13–23ተመልከቱ)።
ይሁን እንጂ ኢሳይያስ የተስፋ መልዕክትም ነበረው። ምንም እንኳን የተተነበየው ጥፋት በእነዚህ መንግሥታት ላይ በመጨረሻ ቢመጣም ኢሳይያስ የመመለስ እና የመታደስ እድልን ተነበየ። እግዚአብሔር ህዝቦቹን ወደ እርሱ እንዲመለሱ ይጋብዛል። “ደረቂቱን ምድር ኩሬ፣ የጥማት መሬት የውኃ ምንጭ” እንዲሆን ያደርጋል” (ኢሳይያስ 35፥7)። ለእስራኤላውያን ቃል የገባላቸውን በረከቶች በመመለስ “ድንቅ ነገርን እና ተአምራትን” ያደርጋል (ኢሳይያስ 29፥14)። ኢሳይያስ ወይም በዛ ሰዓት በሕይወት ያለ ማንኛውም ሰው ይህን ድንቅ ነገር ለማየት አልቻሉም። ነገር ግን ዛሬ እያየነው ነው። በእርግጥም የእሱ አካል ነን!
በቤት እና በቤተክርስቲያን ለመማር የሚረዱ ሃሳቦች
ኢሳይያስ 13፥1–11፣ 19–22፤ 14፥1–20
ኩራትና ዓለማዊነት አይሳካላቸውም።
በኢሳይያስ ዘመን፣ ባቢሎን ኃያል ንጉሥ የነበረባት ኃያል መንግሥት ነበረች። አሁን ባቢሎን ጥንታዊ ታሪክ ናት። ስለዚህ ኢሳይያስ 13–14፣ ለባቢሎን የተነገረው መልዕክት ዛሬ ለእኛ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ባቢሎን ዛሬም በዙሪያችን ያሉ የኩራት ፣ የስግብግብነትና የኃጢአት ምሳሌዎችን ስለምትከተል ነው። ኢሳይያስ 13፥1–11፣ 19–22፤ 14፥1–20ን ሲያነቡ የዚህን ምልክት ያስቡ። እንደእነዚህ ዓይነት ጥያቄዎችንም ማሰብ ትችላላችሁ፦
-
በባቢሎን ንጉሥ ኩራት እና በሰይጣን ኩራት መካከል ምን ዓይነት ተመሳሳይነትን ያያሉ? ( ኢሳይያስ 14፥4–20፤ ሙሴ 4፥1–4ይመልከቱ)። በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ለራሶ ምን ዓይነት ማስጠንቀቂያዎችን ያገኛሉ?
-
አዳኙ እንዴት ነው “ከሃዘን እና ከመከራ … [የሚያሳርፈን]”? (ኢሳይያስ 14፥3)።
“ሞትን ለዘላለም በማሸነፍ ይውጠዋል“ (ኢሳይያስ 25፥8)።
ኢሳይያስ 22፥22–23፤ 24፥21–23፤ 25:6–8፤ 26፥19፤ 28፥16
ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል የተገባው መሲህ ነው።
የኢሳይያስ ትምህርቶች ብዙውን ጊዜ የሃጢያት ክፍያውን፣ ትንሳኤውን እና ዳግም ምፅአቱን ጨምሮ የአዳኙን ተልዕኮ ይጠቅሳሉ ። የሚከተሉትን ጥቅሶች ስታነቡ ምን ዓይነት የተልዕኮ ገፅታዎች ወደ አዕምሯችሁ ይመጣል፦ ኢሳይያስ 22፥22–23፤ 24፥21–23፤ 25፥6-8፤ 26፥19፤ 28፥16? ስለአዳኙ የሚያስታውሶትን ሌሎች ምን ምንባቦች ያገኛሉ?
ምስክርነታቸውን እንዲያካፍሉ ለተማሪዎች ዕድል ስጧቸው። “የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አስተማሪ መሆን ማለት ሌሎች ትምህርቶቹን፣ የቤዛነት ኃይሉን እና ፍፁም ፍቅሩን እንዲረዱና እንዲተማመኑበት ማገዝ ማለት ነው” (በአዳኘ መንገድ ማስተማር፣ 8)። ይህን ማድረግ የሚቻልበት አንዱ ቀላል መንገድ በምታስተምሩበት ጊዜ ሁሉ እንደሚከተለው ያለ ጥያቄ መጠየቅ ነው “በዚህ ሳምንት ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ስለ አዳኝ የተማራችሁት ነገር ምንድን ነው?” ከዚያም ተማሪዎች ተሞክሯቸውን እንዲያካፍሉ እና አንዳቸው የሌላቸውን እምነት እንዲያጠናክሩ ፍቀዱላቸው።
ኢሳይያስ 24፥1–12፤ 28፥1–8፤ 29፥7–13፤ 30፥8–14
ከጌታ መራቅ መንፈሳዊ አደጋን ያስከትላል።
እግዚአብሔር በምሕረቱ ኢሳይያስን የላከው የቃል ኪዳኑን ሕዝብ ከእሱ እየራቁ መሆናቸውን እንዲያስጠነቅቃቸው ነው። ከዚህ ጋር የተያያዙ መንፈሳዊ የማስጠንቀቂያ ምልክቶችን በኢሳይያስ 24፥5፤ 29፥13፤ 30፥8-12 ላይ ማግኘት ትችል እንደሆነ ተመልከት። እነዚህ አመለካከቶች እና ድርጊቶች በመንፈሳዊ አደገኛ የሆኑት ለምንድን ነው?
ኢሳይያስ ከጌታ መራቅ የሚያስከትለውን መዘዝ ለማስጠንቀቅ አንዳንድ የማይረሱ ንፅፅሮችን ተጠቅሟል። እነሱን ስታጠኗቸው ከጌታ መራቅ ምን እንደሚመስል እራሳችሁን ጠይቁ፦
-
አሳዛኝ፣ ባዶ ምድር (ኢሳይያስ 24፥1-12)።
-
ሰካራምነት ኢሳይያስ 28፥7–8።
-
ረሃብ እና ጥማት ኢሳይያስ 29፥7-10።
-
የፈረሠ ቅጥር ወይም የተሰበረ ማድጋ (ኢሳይያስ 30፥13-14)።
ወደ ጌታ መቅረብ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
ኢሳይያስ 29፤ 30፥18-26፤ 35
እግዚአብሔር የጠፉ ወይም የተሰበሩ ነገሮችን ወደነበሩበት መመለስ ይችላል።
ዳግመኛ እንደማታገኙት ያሰባችሁት ነገር ጠፍቶባችሁ ያውቃል? ወይም የሆነ ነገር ተሰብሮና በጭራሽ ሊጠገን እንደማይችል ሰግታችሁ ይሆናል። ከጌታ ስንርቅ ሰይጣን መቼም ቢሆን መመለስ ወይም መፈወስ እንደማንችል እንድናስብ ይፈልጋል። ይሁን እንጂ ኢሳይያስ ጌታ ወደ እርሱ እንድንመለስ ለመርዳት የሚያደርጋቸውን አንዳንድ አስደናቂ ነገሮችን ገልጿል። ከ ኢሳይያስ 29፥13–24፤ 30፥18–26፤35 ስለጌታ፣ ስለፍቅሩ እና ስለኃይሉ ምን ትማራላችሁ? ምናልባትም ፈውስ በሚያስፈልጋችሁ ጊዜ ተስፋ የሚሰጣችሁን ሐረግ በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ልታገኙ ትችላላችሁ። በተጨማሪም እህት ኤሚ ኤ ራይት “Christ Heals That Which Is Broken[ክርስቶስ የተሰበረውን ይፈውሳል]፣” (ሊያሆና፣ ግንቦት 2022(እ.አ.አ), 81-84) የሚለውን መልእክት መመልከት ትችላላችሁ።
ጌታ ኃይሉን እና ምህረቱን ከሚገልፅበት መንገድ አንዱ ወንጌሉን ዳግም መመለሱ ነው። ኢሳይያስ 29 ከዳግም መመለስ ክስተቶች ጋር የሚዛመዱ በርካታ ምንባቦችን ይዟል። ለምሳሌ፦
-
ኢሳይያስ 29፥11–12 ከ 2ኛ ኔፊ 27፥6–26 እና የጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክ 1፥63–65አነፃፅሩ።
-
ኢሳይያስ 29፥13–14 ከ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 4 እና የጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክ 1፥17–19አነፃፅሩ።
-
ኢሳይያስ 29፥18–24 ከ መጽሐፈ ሞርሞን የርዕስ ገፅያነፃፅሩ።
በእናንተ አመለካከት “አስደናቂ” እና “ድንቅ”(ኢሳይያስ 29፡14) የሚሉት ቃላት ጌታ ወንጌሉን ወደ ነበረበት እንደሚመልስ ለመግለጽ ጥሩ ቃላት የሆኑት ለምንድን ነው? ስለ ዳግም መመለስ የተነገሩት ትንቢቶች እንዲፈፀሙ መርዳት የምትችሉት እንዴት ነው? በተጨማሪም ጌሪት ደብሊው ጎንግ፣ “All Nations, Kindreds, and Tongues፣” ሊያሆና ህዳር 2020 (እ.አ.አ)፣ 38-41።
በተጨማሪም “የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ሙላት ዳግም መመለስ፦ ለሁለት መቶኛ አመት መታሰቢያ ለአለም የተላለፈ አዋጅ፣” (ወንጌል ላይብረሪ) “The Morning Breaks [የማለዳ ዕረፍት]፣” መዝሙር፣ ቍጥር 1።
ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የሊያሆና እና የለወጣቶች ጥንካሬ መጽሔቶች ዕትሞችን ተመልከቱ።
ልጆችን ለማስተማር የሚረዱ ሀሳቦች
ኢሳይያስ 14፥3፤ 25፥8–9፤ 28፥16
ኢየሱስ ክርስቶስ ከኃጢያት እና ከሞት ያድነኛል።
-
ልጆቻችሁ በኢሳይያስ መጻሕፍት ውስጥ የሚገኘውን አዳኝ እንዲመለከቱ መርዳት የምትችሉት እንዴት ነው? በኢሳይያስ 14፥3፤ 25፥8፤ ወይም 28፥16 ስለ እሱ የሚያስታውሷችሁን ሐረጎች እንዲያገኙ ልትረዳቸው ትችላለህ። በተጨማሪም እነዚህን ከኢሳይያስ የተወሰዱ ጥቅሶች እንደ ማቴዎስ 11:28–30፤ 1 ቆሮንቶስ 15:53–57፤ ሄለማን 5:12 ካሉ ስለ አዳኙ ከሚያስተምሩ ሌሎች ጥቅሶች ጋር ማወዳደር ይችሉ ነበር። ጌታ ምን ታላቅ ነገር አድርጎልናል?
-
ኢሳይያስ 25፡8–9ን በጋራ ካነበባችሁ በኋላ አዳኙ በጌቴሴማኒ፣ በመስቀል ላይ እና ከትንሳኤው በኋላ የተሳሉትን ስዕሎች መመልከት ትችላላችሁ። ልጆቻችሁ በሥዕሎቹ ላይ ምን እየተደረገ እንዳለ እንዲሁም ኢየሱስን የሚወዱትና “በደኅንነቱ የሚደሰቱት” ለምን እንደሆነ እንዲናገሩ አድርጉ።(ቁጥር 9)
-
የምትወዱት ሰው ሲሞት ስለተሰማችሁት ሀዘን ለልጆቻችሁ መናገር ትመርጡ ይሆናል። በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ስለተቀበላችሁት መፅናኛ ምስክርነት ስጡ። ምናልባትም ልጆቻችሁ የሚያለቅሱ ፊቶችን በመሳል ኢሳይያስ 25፡ 8ን በጋራ ስታነቡ እንባውን ማጥፋት ትችሉ ይሆናል።
ፈቃድህ ይፈጸም፣ በኬን ስፔንሰር
ኢሳይያስ 25፥4–6
ኢየሱስ “ከአውሎ ነፋስ መሸሸጊያ” ሰጥቶናል።
-
እናንተም ሆነ ልጆችቻችሁ በዐውሎ ነፋስ ወይም በሞቃት የበጋ ቀን ጥላ ሥር በመሆን በረከት አግኝታችኋል? ወይም ተርባችሁ ሳለ ጥሩ ምግብ በልታችሁ ታውቃላችሁ? ኢሳይያስ 25፥4-6ን ስታነቡ ስለእነዚህ ተሞክሮዎች ተነጋገሩ። ኢየሱስ ከእነዚህ ነገሮች ጋር የሚመሳሰለው እንዴት ነው?
ኢሳይያስ 29፥11፣ 11–18፣ 24
የወንጌል ዳግም መመለስ “አስደናቂ ሥራ” ነው።
-
ኢሳይያስ 29፣14ን ከልጆቻችሁ ጋር ስታነቡ “አስደናቂ” እና “ድንቅ” ከሚሉት ቃላት ጋር ተመሳሳይ ትርጕም ያላቸውን ሌሎች ቃላት አካፍሏቸው። በመጨረሻው ዘመን የጌታን ድንቅ ሥራዎች የሚወክሉ ነገሮችን ወይም ስዕሎችን እንድታገኙ ይርዷችሁ። እነዚህም የመጽሐፈ ሞርሞን ቅጂ፣ የቤተመቅደስ ስዕል፣ ወይም የመጀመርያው ራእይ ስዕል (በዚህ መፅሐፍ መጀመሪያ አለ) ሊያካትቱ ይችላሉ። ከዚያም ልጆቻችሁ አንድን ዕቃ በመምረጥ ለእነሱ አስደናቂ የሆነበትን ምክንያት ሊነግሯችሁ ይችላሉ።
-
ስለተመለሰው ወንጌል የሚያወሳ መዝሙር ከኢሳይያስ 29 ጋር በጥሩ ሁኔታ ሊሄድ ይችላል፣ ለምሳሌ “On a Golden Springtime [በወርቃማው የፀደይ ወቅት]” (የልጆች መዝሙሮች መጽሐፍ፣ 88)። እና ምናልባት አንድ የግል ተሞክሮ ልጆቹ ዳግም መመለስ ማለት ምን ማለት እንደሆነ እንዲገነዘቡ ሊረዳቸው ይችላል። ለምሳሌ እናንተ እና ልጆቻችሁ የጠፋባችሁን ነገርና እንዴት እንዳገኛችሁት መነጋገር ትችላላችሁ። ልጆቻችሁ ይህንን ከወንጌል ዳግም መመለስ ጋር እንዲያነጻጽሩ እርዷቸው። በኢሳይያስ 29፥13-15፣ መሠረት ወደ ቀድሞ ኹኔታችን መመለስ የሚያስፈልገን ለምንድን ነው? ጌታ ወንጌሉን ለማደስ ምን ድንቅ ስራዎችን እያከናወነ ነው?( የዚህ ሳምንት ዝግጅት ገጽ ተመልከት)
ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የጓደኛ መጽሔት ዕትም ተመልከቱ።