“ልናስታውሳቸው የሚገቡን ሀሳቦች፦ ነብያት እና ትንቢት፣” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ) [2026 (እ.አ.አ)]
“ነብያት እና ትንቢት፣” ኑ፣ ተከተሉኝ፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ)
ልናስታውሳቸው የሚገቡን ሀሳቦች
ነብያት እና ትንቢት
በብሉይ ኪዳን የተለምዶ የክርስቲያን ክፍል ውስጥ የመጨረሻው ክፍል (ከኢሳይያስ እስከ ሚልክያ) “ነብያቶች” ተብሎ ይጠራል። የብሉይ ኪዳን አንድ አራተኛ የሆነው ይህ ክፍል ስልጣን ያላቸውን የእግዚአብሔር አገልጋዮች ቃላት ይዟል፣ እነርሱም ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋገሩ ከዚያም ስለ እርሱ ተናገሩ፣ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ900 እና 500 ዓመታት መካከል የእርሱን መልዕክት ለህዝቦች አካፈሉ።
ነቢያት የእግዚአብሄርን ፈቃድ ይገልጻሉ።
ነብያት እና ትንቢት በመላ ብሉይ ኪዳን ውስጥ ታላቅ ሚናን ይጫወታሉ። አብርሐም፣ ይስሃቅ እና ያዕቆብ ራዕዮችን ተመለከቱ እንዲሁም ከሰማይ መልዕክተኞች ጋር ተነጋገሩ። ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ፊት ለፊት ተነጋገረ እንዲሁም ለእስራኤል ልጆች ያለውን ፍቃድ አስታወቀ። የቀዳማዊ እና የካልዕ ነገሥት መጽሐፎች የነብያት ኤልያስን እና የኤልሳዕን የሚታወሱ ስራዎች እና መልዕክቶች ይዘግባሉ። ብሉይ ኪዳን እንደ ማሪያም እና ዲቦራ፣ እንዲሁም እንደ ርብቃ እና ሐና ያሉ በትንቢት፣ መንፈስ የተባረኩ ሌሎች ሴቶች ተጠቅሷል። ምንም እንኳን መዝሙረ ዳዊት በመደበኛ ነቢያት ባይፃፍም በተለይ የመሲሁን መምጣት ስለሚጠብቅ በትንቢት መንፈስ የተሞላ ነው።
ከእነዚህ የትኛውም የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አባላትን አያስገርማቸውም። በእርግጥ፣ ነብያት የታሪክ አስገራሚ ትንሽ ክፍል ብቻ ሳይሆኑ የእግዚአብሔር ዕቅድ አሰፈላጊ አካል እንደሆኑ የተመለሰው የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ያስተምረናል። የተወሰኑ ሰዎች ነብያትን ለብሉይ ኪዳን ዘመን የተለዩ አድርገው ሊመለከቱ ቢችሉም እኛ ከብሉይ ኪዳን ጊዜዎች ጋር በጋራ እንዳለን ነገር አድርገን እናያቸዋለን።
ከኢሳይያስ ወይም ከሕዝቅኤል አንድን ምዕራፍ ማንበብ ከወቅታዊው የቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት የአጠቃላይ ጉባኤ መልዕክትን ከማንበብ የተለየ መስሎ ሊሰማን ይችላል። አንዳንድ ጊዜ የጥንት ነብያት ለእኛ የሚናገሩት ነገር አለ ብለን ለማየት ከባድ ሊሆን ይችላል። ደግሞም፣ ዛሬ የምንኖርበት ዓለም እነርሱ ከሰበኩበት እና ከተነበዩበት ጋር በጣም የተለየ ነው። በሕይወት ያለ ነብይ በእርግጥ ስላለን ጥያቄን ያስነሳል፦ ጥረቱ ተገቢ የሆነው ለምንድን ነው—እንዲሁም የጥንት ነብያትን ቃላት ለማንበብ ጥረት የሚፈልገው ለምንድን ነው?
የጊዜዎች ሙላት፣ በግሬግ ኦልሰን
ለእኛ የሆነ የሚናገሩት ነገር አላቸው
በአብዛኛው ክፍል፣ ዛሬ ሰዎች የብሉይ ኪዳን ነብያት ዋነኛ ታዳሚዎች አይደሉም። እነዚያ ነብያት በሰዓታቸው እና በቦታቸው ወቅታዊ ችግሮችን እየገለፁ ነበር—ልክ እንደኋለኛው ቀን ነብያት ወቅታዊ ችግሮቻችንን ዛሬ እንደሚገልፁት።
በተመሳሳይ ጊዜ፣ ነብያት ከወቅታዊ ችግሮች ባሻገር ሊመለከቱ ይችላሉ። ለማንኛውም እድሜ ተገቢ የሆነውን የዘላለም እውነቶች ያስተምራሉ። እናም፣ በራዕይ በመባረክ ትልቁን ምስል፣ የእግዚአብሔርን ስራ ስፋት ይመለከታሉ። ለምሳሌ፣ ኢሳይያስ በዘመኑ የነበሩትን ሰዎች ስለ ኃጢአታቸው አስጠንቅቋቸዋል። በተጨማሪም ከ200 ዓመታት በኋላ የሚኖሩ እስራኤላውያን ነጻ እንደሚወጡ ጽፏል። በተመሳሳይም የአምላክ ህዝቦች በሙሉ ስለሚፈልጉት መዳን አስተምሯል። በተጨማሪም፣ ዛሬ እራሱ ሙሉ በሙሉ መከናወናቸውን እየጠበቁ ያሉ—እንደ የ“አዲስ ምድር” ቃልኪዳን (ኢሳይያስ 65፥17) “እግዚአብሔርን በማወቅ የተሞላች” ስለሆነች (ኢሳይያስ 11፥9) የጠፉት የእስራኤል ነገዶች ተሰብስበው እና “ሕዝብ” “ሰልፍም ከእንግዲህ ወዲህ [እንደማይኖር]” ትንቢቶችን ሊፅፍ ይችላል (ኢሳይያስ 2፥4)። ልክ እንደኢሳይያስ ዓይነት የብሉይ ኪዳን ነብያቶችን ቃላት በማንበብ የሚመጣ ደስታ እና መነሳሳት አንዱ አካል እኛ እነሱ በተመለከቱት ክብራዊ ቀን ውስጥ ሚና እንደተጫወትን መገንዘብ ነው።
ስለዚህ የጥንት ትንቢቶችን ስታነብ የተጻፉበትን አውደ-ጽሑፍ ማወቅ ሊረችሁ ይችላል፣ ነገር ግን እናንተ በእነሱ ውስጥ ራሳችሁን ማየት አለባችሁ፣ ወይም “ከእነርሱ ጋር [ከራችሁ] ጋር ማመሳሰል” (1 ኔፊ 19፥24፤ በተጨማሪም ቁጥር 23ን ተመልከት)። አንዳንድ ጊዜ ባቢሎንን እንደ ጥንት ከተማ ብቻ ሳይሆን አንደ ዓለማዊነት እና የኩራት ምልክት አድርጎ መገንዘብ ማለት ነው። እስራኤልን በማንኛውም ጊዜና ቦታ እንደ እግዚአብሔር ሕዝብ መረዳት ማለት ሊሆን ይችላል። ወይም ደግሞ ጽዮንን ለኢየሩሳሌም ሌላ ስም አድርጎ ከመመልከት ይልቅ የአምላክ ህዝቦች የሚቀበሏት የኋለኛው ዘመን ዓላማ አድርጎ ማየት ማለት ሊሆን ይችላል።
ቅዱሳን መጽሐፍትን ማመሳሰል እንችላለን ምክንያቱም አንድ ትንቢት በብዙ መንገዶች እንደሚከናወን ስለምናውቅ። የዚህ ጥሩ ምሳሌ በ ኢሳይያስ 40፥3፤ ውስጥ ያለው ትንቢት ነው፦ “የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፣ ለአምላካችንም ጎዳና በበረሀ አስተካከሉ።” በባቢሎን ውስጥ በምርኮ ለተያዙት አይሁዶች ይህ መግለጫ እግዚአብሔር ከምርኮ የሚወጡበትን እና ወደ ኢየሩሳሌም የሚመለሱበትን መንገድ እየሰጠ እንዳለ ሊገልፅ ይችላል። ለማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ እና ሉቃስ ይህ ትንቢት የአዳኙን ምድራዊ አግልግሎት መንገድ ባዘጋጀው በመጥምቁ ዮሐንስ ውስጥ ተከናውኗል። እና ጆሴፍ ስሚዝ ይህ ትንቢት በኋለኞቹ ቀናት ለክርስቶስ የሺህ ዓመታት አገልግሎት ዝግጅት አሁንም እየተከናወነ እንደሆነ መገለጥን ተቀበለ። በተወሰነ መልኩ የጥንት ነብያት ለእኛ በእርግጥ እንደተናገሩ ለመረዳት አሁንም እየቀረብን ነው። ለጥንት እስራኤል የሚዛመዱ እንደሆኑ ሁሉ ለእኛም የሚዛመዱ ብዙ ውድ፣ ዘላለማዊ እውነቶችን አስተማሩ።
የጥንት ነቢያት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መስክረዋል።
ምናልባት እራሶን በብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ውስጥ ከማየት የበለጠ ጠቃሚ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስን በእነሱ ውስጥ ማየት ነው። እርሱን ከፈለጉ ያገኙታል፣ ምንም እንኳን በስም ባይጠራም። የብሉይ ኪዳኑ እግዚአብሔር፣ ጌታ ይሆዋ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ማስታወስ ሊረዳ ይችላል። በማንኛውም ጊዜ ነብያቶች እግዚአብሔር እያደረገ ስላለው ነገር ወይም ስለሚያደርገው ነገር ሲገልፁ ስለአዳኙ እየተናገሩ ነው።
ጌታ ለአብርሃም ሲገለጥ፣ በኪዝ ላርሰን
እንዲሁም ስለተቀባው፣ ቤዛ እና ከዳዊት ዘር ስለሚመጣው የወደፊት ንጉሥ መግለጫን ታገኛላችሁ። እነዚህ በሙሉ ስለኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገሩ ትንቢቶች ናቸው። በአጠቃላይ ነፃ ስለመውጣት፣ ይቅርታ፣ ቤዛነት እና መመለስ ያነባሉ። አዳኙ በአዕምሮዎ እና በልቦ ውስጥ ሲኖር እነዚህ ትንቢቶች እንደሚጠበቀው ወደ እግዚአብሔር ልጅ ይጠቁሞታል። ትንቢትን የመረዳት ምርጡ መንገድ “የትንቢት መንፈስ” ማግኘት ነው እሱም “የኢየሱስ ምስክር” እነደሆነ ዮሐንስ ነግሮናል (ራዕይ 19፥10)።