ኑ፣ ተከተሉኝ
መስከረም 14–20 (እ.አ.አ) “አምላክ መድሀኒቴ ነው”፦ ኢሳይያስ 1–12


“መስከረም 14-20። ‘አምላክ መድሀኒቴ ነው’፦ ኢሳይያስ 1–12፣” ኑ፣ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ) 2026 (እ.አ.አ)

“መስከረም 14-20። “አምላክ መድሀኒቴ ነው’ ” ኑ፣ ተከተሉኝ፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ)

ኢሳይሳስ በብራና ላይ ሲጽፍ

ነብዩ ኢሳይያስ ስለ ክርስቶስ ልደት ተነበየ፣ በሃሪ አንደርሰን

ኢሳይያስ 14-20፦ “አምላክ መድሀኒቴ ነው”

ኢሳይያስ 1–12

ምንም እንኳን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነቡ ይህ የመጀመሪያዎ ቢሆንም አስቀድመው የሚያውቋቸው የሚመስሉ ምንባቦችን ሊያገኙ ይችላሉ። የዚያም ምክንያት፣ ከሁሉም የብሉይ ኪዳን ነብያት መፅሐፈ ኢሳይያስ በሌሎች መጽሐፎች ውስጥ በአዳኙም በራሱ ጭምር ብዙ ጊዜ በመጠቀሱ ምክንያት ነው። የኢሳይያስ ቃላት ብዙ ጊዜ በመዝሙሮች እና በሌሎች ቅዱስ ሙዚቃዎች ውስጥም ይቀርባሉ።

ለምንድን ነው ኢሳይያስ ብዙ ጊዜ የተጠቀሰው? በእርግጥ ከምክንያቶቹ አካል አንዱ መፅሐፈ ኢሳይያስ የእግዚአብሔርን ቃል በግልፅ በሚታወስ ቋንቋ የመግለፅ ስጦታ ስለነበረው ነው። ነገር ግን ከዚያም በላይ ነው። ያስተማራቸው እውነታዎች የእርሱን ትውልድ—ከ740 እስከ 701 ከክርቶስ ልደት በፊት ባሉት አመታት ሲኖሩ የነበሩ እስራኤላዊያንን—በመሻገራቸው ምክንያት ኢሳይያስ በብዙ ትውልዶች ውስጥ የነበሩ ነብያትን አነሳስቷል። የእርሱ ሚና ለእግዚአብሔር የቤዛነት ስራ አይኖቻችንን መክፈት ነበር እሱም ከአንድ አገር ወይም ከአንድ የጊዜ ዘመን የበለጠ ትልቅ ነው። ኔፊ እሱ እና ህዝቦቹ ምንም እንኳን ከተቀሩት እስራኤላውያን ቢለዩም አሁንም ድረስ የእግዚአብሔር የቃልኪዳን ህዝቦች እንደሆኑ ከኢሳይያስ ተማረ። በመፅሐፈ ኢሳይያስ ውስጥ፣ የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ስለ መሲሁ በፊታቸው እየተፈጸሙ ያሉ ትንቢቶችን አገኙ። እናም በመጽሃፈ ኢሳይያስ ውስጥ፣ ጆሴፍ ስሚዝ በኋለኛው ቀን እስራኤልን የመሰብሰብ ስራ እና ጽዮንን የመገንባት መነሳሳትን አገኘ። መጽሃፈ ኢሳይያስን ሲያነቡ ምን ያገኛሉ?

ስለኢሳይያስ እና ጽሑፎቹ የበለጠ መረጃ በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ውስጥ “ኢሳይያስ” የሚለውን ይመልከቱ። ኢሳይያስ ስለኖረበት ጊዜ መረጃን ለማግኘት 2ኛ ነገሥት 15–20 እና 2ኛ ዜና መዋዕል 26–32ን ተመልከቱ።

የጥናት ምልክት

በቤት እና በቤተክርስቲያን ለመማር የሚረዱ ሃሳቦች

ኢሳይያስ 1–12

የኢሳይያስ ቃላት በሙሉ ይፈጸማሉ።

አዳኙ ስለ ኢሳይያስ ሲናገር እንዲህ ብሏል፣ “የተናገራቸው እንዲሁም በተናገራቸው ቃላት መሰረት ሁሉም ነገሮች ሆነዋልም [እንዲሁም] ይሆናሉም ” (3ኛ ኔፊ 23፥3)። የኢሳይያስን መፅሐፍ በምታጠኑበት ጊዜ የሚከተሉትን ርዕሶች ያካተተ የትንቢቶች ሰንጠረዥ ለመሥራት ሞክሩ፦ የኢሳይያስ ዘመንየአዳኙ ሰብአዊ አገልግሎት እና የኋለኛው ዘመን። በርካታ የኢሳይያስ ትንቢቶች ከአንድ በላይ በሆነ መንገድ ፍጻሜያቸውን እንዳገኙ ልብ በሉ (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ “ኢሳይያስ”)።

ፕሬዚዳንት ዳለን ኤች. ኦክስ እንዳስተማሩት፦ “የኢሳይያስ መጽሐፍ ብዙ ፍጻሜ ያላቸው የሚመስሉ በርካታ ትንቢቶችን ይዟል። አንደኛው በኢሳይያስ ዘመን የነበሩትን ሰዎች ወይም በቀጣዩ ትውልድ የነበሩትን ሁኔታዎች የሚመለከት ይመስላል። ሌላው ትርጉሙ ብዙውን ጊዜ ምሳሌያዊ ሲሆን ኢየሩሳሌም ስትጠፋና ህዝቦቿም የእግዚአብሔር ልጅ ከተሰቀለ በኋላ ሲበተኑ የነበሩትን ክስተቶች የሚያመለክት ይመስላል። የትንቢቱ ሌላ ትርጉም ወይም ፍጻሜ አዳኙ ዳግመኛ በሚመጣበት ጊዜ ከሚከሰቱት ክስተቶች ጋር የተያያዘ ይመስላል። ከእነዚህ ትንቢቶች መካከል ብዙዎቹ በርካታ ትርጉሞች ሊኖራቸው እንደሚችል መገንዘባችን የመንፈስ ቅዱስን መገለጥ መጠየቃችን አስፈላጊ መሆኑን ያጎላል። “Scripture Reading and Revelation [የቅዱሳት መጻሕፍት ንባብ እና ራዕይ]፣” ኢንዛይን፣ ጥር. 1995 (እ.አ.አ)፣ 8)።

የቅዱሳት መጻሕፍት ንባብ እና ራዕይ አዳኙ እንዲህ ብሏል፣ “እነዚህን ነገሮች በትጋት [ፈልጉ]፤ … የኢሳይያስ ቃላት ታላቅ ናቸውና” (3ኛ ኔፊ 23፥1፤ እንዲሁም ቁጥር 2–3 ተመልከቱ)። ይሁን እንጂ ለብዙዎች መጽሃፈ ኢሳይያስን መረዳት ከባድ ሊሆን ይችላል። የሚከተሉት ማበረታቻዎች ሊረዳችሁ ይችላሉ፦

  • ኢሳይያስ የተጠቀማቸውን ምልክቶች እና ምሳሌያዊ ንግግሮች ያሰላስሉ።

  • እያንዳንዱን ምዕራፍ ስታነቡ እራሳችሁን “ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምን እየተማርኩኝ ነው?” ብላችሁ ጠይቁ (1ኛ ኔፊ 19፥23 ተመልከቱ)።

  • ለዘመናችን አግባብነት ያላቸው ርዕሰ ጒዳዮችን ፈልጉ።

  • እንደ መዝገበ ቃላት፣ የግርጌ ማስታወሻዎች፣ የምዕራፍ አርዕስቶችና ቅዱሳን መጻህፍት መምሪያ የመሳሰሉትን የመማሪያ መሣሪያዎች ተጠቀሙ።

ኢሳይያስ 13–5

የሴሚናሪ ምልክት
ነቢያት ስለ ኃጢአት ያስጠነቅቃሉ እናም በንስሐ በኩል የቃልኪዳን ተስፋ ያደርጋሉ።

ኢሳይያስ በሁሉም ዘመናት እንደነበሩት ነቢያት ሕዝቡን ስለ መንፈሳዊ ሁኔታቸው ያለማቋረጥ ያስጠነቅቅ ነበር። ኢሳይያስ 135ን ስታነብ ሕዝቡ በመንፈሳዊ ምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንደነበር የሚገልጹ ሐረጎችን ፈልግ።( ለምሳሌ ኢሳይያስ 1፥2–4፣ 21–233፥9 16–175፥11-12, 20-23ን ተመልከት።) በዘመናችን ምን አይነት ተመሳሳይ ችግሮችን ትመለከታላችሁ? በተጨማሪም እስራኤላውያን በመንፈሳዊ ሁኔታ መጐዳታቸው የሚያስከትለውን መዘዝ አስመልክቶ ማስጠንቀቂያ የሚሰጡ ጥቅሶችን መፈለግ ትችላለህ ኢሳይያስ 1፥73፥17-265፥5-7, 13-15

ከማስጠንቀቂያው በተጨማሪ ለእስራኤል የተስፋ መልዕክቶችን ማሳታወሻ መያዝ ይችላሉ (ለምሳሌ፣ ኢሳይያስ 1፥16-19፣ 25–273፥104ን ተመልከቱ)። ከእነዚህ መልዕክቶች ስለጌታ ምን ትማራላችሁ? በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ያለው የጌታ መልዕክት ሰይጣን እንድናምን ከሚፈልገው ጋር የሚለየው እንዴት ነው?

በዛሬው ጊዜ ያሉ ነቢያትም እንደ ኢሳይያስ ስለ ኃጢአትና የሚያስከትለው መዘዝ ያስጠነቅቁናል፤ እንዲሁም በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት የተስፋ መልእክት ያስተላልፋሉ። ሌሎች ምን ምሳሌዎችን ማሰብ ትችላላችሁ? እንዲህ ያሉ ማስጠንቀቂያዎችን እና ተስፋዎችን ለመፈለግ አንድን የቀድሞ የጠቅላላ ጉባኤ መልእክት መከለስ ትፈልጉ ይሆናል።

ኢሳይያስ 2፤ 411–12

በኋለኛው ቀናት እግዚአብሔር ታላቅ ስራን ይሰራል።

ብዙቹ የኢሳይያስ ጽሑፎች ለኛ ጊዜ ለየት ያለ ትርጉም የያዙ ትንቢቶች ናቸው። እነሱን ለማግኘት የወደፊት ጊዜ ግሶችን( እንደ “መሆን አለበት” ወይም “መሄድ አለበት”) ይፈልጉ። ለምሳሌ ያህል፣ ኢሳይያስ 2⁠411-12ን ስታነብ እነዚህን ግሦች ፈልግ። እንዲያውም በወቅታዊ ግሦች( እንደ ነው ወይም እየሄደ ነው) ለመተካት ልትሞክሩ ትችላላችሁ። በተለይ አስደሳች የሆኑት የትኞቹ ትንቢቶች ናቸው? ስለ ጽዮን፣ ስለ ቤተ መቅደሶች ግንባታና ስለ እስራኤል መሰብሰብ ከሚናገሩት ትንቢቶች ምን ትምህርት አግኝታችኋል?

ኢሳይያስ 2፡23 በተለይ ለኋለኛው ቀን ቅዱሳን ጠቃሚ ነው። እነዚህ ትንቢቶች እየተፈጸሙ ያሉት እንዴት ነው? (ከቁጥር 3) ውስጥ ስለጌታ ነቢያት እና ስለ ራዕዮች ምን ትማራላችሁ?

በተጨማሪም “ኢሳይያስ 5፥26፤” “በተራራው ከፍታ ላይ [High on the Mountain Top]፣” መዝሙር፣ ቁጥር 5 ተመልከቱ።

ትንቢተ ኢሳይያስ 6

ነብያት በእግዚአብሔር የተጠሩ ናቸው።

ኢሳይያስ 6፣ ውስጥ ኢሳይያስ ነብይ ሆኖ የተጠራበትን ሁኔታ ገልጿል። ይህን ምዕራፍ ሲያነቡ ኢሳይያስ ስላጋጠመው ነገር ምን አስደነቆት? ይህ ምዕራፍ ስለእግዚአብሔር፣ ስለነብያቶቹ እና እንዲሰሩ ስለተጠሩት ስራ በሚያስቡበት መንገድ ላይ እንዴት ተፅዕኖ ያደርጋል?

ማርያም ከህፃኑ ኢየሱስ ይዛ

“ህፃንም ተወልዶልናልና፣ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና” (ኢሳይያስ 9፥6)።

ኢሳይያስ 7–9

እግዚአብሄር አዳኛችን እንዲሆን ኢየሱስ ክርስቶስን እንደሚልክልን ቃል ገብቶልናል።

በኢሳይያስ ዘመን እስራኤል ራሷን ከአሦር ለመከላከል ከሶርያ ጋር ቃል ኪዳን ገባች። እስራኤል እና ሶሪያ የይሁዳውን ንጉሥ አካዝን የእነሱን ህብረት እንዲቀላቀል ለመግፋት ፈለጉ። ነገር ግን ህብረቱ እንደሚወድቅ ኢሳይያስ ተነበየ እናም አካዝን በእግዚአብሔር እንዲያምን መከረው (ኢሳይያስ 7፥7–98፥12–13ተመልከቱ)።

ኢሳይያስ አካዝን ሲመክር ብዙ ታዋቂ የሆኑ ትንቢቶችን አደረገ እነሱም በ ኢሳይያስ 7፥148፥13–149፥2, 6–7ውስጥ ይገኛሉ። እነዚህ ትንቢቶች ለአካዝ ምንም ትርጕም ቢኖራቸውም በግልጽ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ተፈጻሚነት አላቸው (እንዲሁም ማቴዎስ 1፥21–234፥1621፥44ሉቃስ 1፥31–33ተመልከቱ)። “አማኑኤል” የሚለው ስያሜ ለአዳኙ ተስማሚ የሆነው ለምንድን ነው? (ማቴዎስ 1፥23ተመልከቱ)። ለናንተ “ማካሪ” ወይም “የሰላም ልኡል” የሆነው እንዴት ነው? (ኢሳይያስ 9፥7)። ከእነዚህ ጥቅሶች ስለ አዳኙ ሌላ ምን ትማራላችሁ?

ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የሊያሆና እና የለወጣቶች ጥንካሬ መጽሔቶች ዕትሞችን ተመልከቱ።

የልጆች ክፍል ምልክት 

ልጆችን ለማስተማር የሚረዱ ሀሳቦች

ኢሳይያስ 1፥2–4፤ 16–19።

በኢየሱስ ክርስቶስ ምክንያት ንስሐ ገብቼ ንጹሕ መሆን እችላለሁ።

  • ኢሳይያስ 1፡24፣ ላይ እናንተና ልጆቻችሁን ጌታ በሕዝቡ ደስተኛ ያልሆነበትን ምክንያት ማግኘት ትችላላችሁ። በቍጥር 3 ላይ ከእንስሳት ጋር የተደረገውን ማነጻጸር ልብ በሉ፦ “ጌታችን” ማን ነው? እንደምናውቅ ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው?

  • ኢሳይያስ 1፥16-18፣ በዓይነ ሕሊናችሁ ለመሳል እናንተ እና ልጆቻችሁ ደማቅ ቀይ የሆነን ነገርና ንጹሕ ነጭ የሆነን ነገር መመልከት ትችላላችሁ። ወይም ደግሞ አንድ ነገር ለመታጠብ አብራችሁ መሥራት ትችላላችሁ። ያልተቀደሰ ልንሆን የምንችለው እንዴት ነው? ኢየሱስ እንድንነፃ የሚረዳን እንዴት ነው? . ከእነዚህ ጥቅሶች ስለ አዳኙ ምን እማራለሁ? ስለ እሱ ምን እንደሚሰማችሁ እና ለእናንተ ስላደረጋቸው ነገሮች ለልጆቻችሁ አካፍሏቸው።

ኢሳይያስ 2፥2–4

በቤተ መቅደስ፣ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እማራለሁ።

  • ኢሳይያስ ቤተ መቅደስን “የጌታ ቤት ተራራ” ብሎ ጠርቷል (ኢሳይያስ 2፥2)። ልጆቻችሁ ወደ ጌታ ቤት በመሄዳቸው እንዲደሰቱ መርዳት የምትችሉት እንዴት ነው? የቤታቸውን ስዕል እንዲስሉ ልትጋብዟቸው ትችላላችሁ። ኢሳይያስ 2፥2ን በጋራ አንብቡ፤ ከዚያም “የጌታ ቤት” ማለትም ቤተ መቅደስ ምን እንደሚመስል ስዕል እንዲስሉ ጋብዟቸው። ኢሳይያስ 2፥3ን በጋራ አንብቡ። የቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ ወደ ቤተመቅደሱ የሚመጡ ብዙ ሰዎችን በፎቶዎቻቸው ላይ እንዲጨምሩ ጋብዙ።

  • በተጨማሪም ኢሳይያስ 2፥23ን በጋራ ማንበብና እናንተም ሆናችሁ ልጆቻችሁ ወደ ቤተ መቅደሱ እንድትሄዱ የሚያነሳሳችሁን አንድ ሃሳብ መናገር ትችላላችሁ። ከዚያም ኢሳይያስ 2፥4ን በጋራ ካነበባችሁ በኋላ የሰማዩ አባት እና ኢየሱስ ስለ እኛ የሚያውቋቸውን ነገሮች ዘርዝሩ። ስለ ቤተመቅደስ መዝሙር ለመዘመር አስቡ፣ ለምሳሌ “ቤተመቅደስን ማየት እወዳለሁ” (የልጆች መዝሙር፣ 95)። በመዝሙሩ ውስጥ ቤተመቅደስ ምን እንደሆነ እና እዚያ ምን እንደምናደርግ የሚያስተምሩ ሃረጎችን እንዲያገኙ እርዷቸው።

የሶልት ሌክ ቤተመቅደስ አመሻሽ ላይ

የሶልት ሌክ ቤተመቅደስ

ኢሳይያስ 7፥149፥6–7

ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኜ ለመሆን ወደዚህ ምድር መጣ።

  • ኢሳይያስ ስለ ክርስቶስ የተናገራቸውን ትንቢቶች ለማስተዋወቅ እናንተ እና ልጆቻችሁ ስለ ሰዎች የማዕረግ ስሞች ለምሳሌ ፕሬዚዳንት፣ ጳጳስ ወይም አስተማሪ መወያየት ትችላላችሁ። እነዚህ ቃላት ስለ ሰዎቹ ምን ይነግሩናል? ልጆቻችሁ በኢሳይያስ 7፥14 እና 9፥6-7 ላይ የኢየሱስ ክርስቶስን የማዕረግ ስሞች እንዲያገኙ እርዷቸው (የዚህ ሣምንት የአክቲቪቲ ገፅ ተመልከቱ)። እያንዳንዱ ርዕስ ስለ እሱ ምን ያስተምረናል? ከእነዚህ ጥቅሶች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምን እንማራለን?

  • በተጨማሪም ለልጆቻችሁ “ነቢዩ ኢሳይያስ” (በብሉይ ኪዳን ታሪኰች፣ 150-51ን ) ማካፈል ትችላላችሁ ኢሳይያስ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመወለዱ ከብዙ ዓመታት በፊት ስለ እሱ ምን ያውቅ እንደነበር ለማወቅ በየጊዜው እያቆማችሁ ጠይቁ። ከዚያም በኢሳይያስ 7፥149፥6-7 ላይ የሚገኙት የኢሳይያስ ትንቢቶች እንዴት እንደተፈጸሙ ለማብራራት ማቴዎስ 1፥21-23ሉቃስ 1፥31-33ን ልትጠቀም ትችላለህ።

    1:18

    Isaiah the Prophet

ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የጓደኛ መጽሔት ዕትም ተመልከቱ።

ከቤተ መቅደሱ በላይ በሰማይ ላይ መብረቅ ብልጭታ።

ቤተ አምልኮ “ጥላ” እና “ከአውሎ ነፋስና ከዝናብ መሸሸጊያ” እንደሚሆን ኢሳይያስ አስተማረ (ኢሳይያስ 4፥6)። የአይዳሆ ፎልስ አይዳሆ ቤተመቅደስ

ዋና የእንቅስቃሴ ገጽ፦ አሳይያስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መሰከረ።