ኑ፣ ተከተሉኝ
ሰኔ 29–ሐምሌ 5 (እ.አ.አ)፥ “እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ”፡ 1 ነገሥት 12–13፤ 17–22


“ሰኔ 29–ሐምሌ 5 (እ.አ.አ)። “እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ”፡ 1 ነገሥት 12–13፤ 17–22 “.ኑ፥ ተከተሉኝ—ለቤት እና ለቤተክርስቲያን፦ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ) [2026 (እ.አ.አ)]

“ሰኔ 29–ሐምሌ 5 (እ.አ.አ)። ‘እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ’” ኑ፣ ተከተሉኝ፡ ብሉይ ኪዳን 2026 (እ.አ.አ)

ኤሊያስ በሚቃጠል መስዋዕት ፊት

ኤልያስ ከበኣል ካህን ጋር ሲሟገት፣ በጄሪ ሃርስተን

ሰኔ 29–ሐምሌ 5 (እ.አ.አ)፡ “እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ”

1 ነገስት 12–1317–22

የእስራኤል ቤት ግራ በመጋባት ላይ ነበረች። አስሩ ነገዶች የሰሜኑን የእስራኤል መንግስት፣ ሁለቱ ነገዶች ደግሞ የደቡቡን የይሁዳ መንግስት በመመስረት የእስራኤል መንግስት ተከፋፍሎ ነበር። ነገር ግን እርስ በእርሳቸው ከመለያየታቸው የከፋው ሁለቱም መንግስታት ከቃል ኪዳናቸው መለየታቸው ነበር። ክፉ ነገሥታት ሕዝቡን ከጌታ አራቁ እንዲሁም ብዙ ሰዎች በእምነታቸው የሚወላውሉ ሆኑ።

በዚህ ሁኔታ ውስጥ፣ ጌታ ኤልያስን ነቢይ አድርጎ ጠራው። የሱ ህይወት የሚያሳየው አንድ ሰው በመጥፎ ሁኔታዎች ውስጥ ቢሆንም እንኳን በጌታ ላይ ታላቅ እምነት ሊኖረው እንደሚችል ነው። አንዳንድ ጊዜ ጌታ እንደዚህ ላለው እምነት በአስደናቂ፣ ከሰማይ እንደሚወርድ እሳት ባለ የአደባባይ ተአምራት ምላሽ ይሰጣል። ነገር ግን አንዲት ታማኝ መበለትን እና ልጇን እንደመመገብ ያሉ ጸጥ ያሉ ተአምራትንም ይሰራል። ብዙ ጊዜ የጌታ ተአምራት ግላዊ ከመሆናቸው የተነሳ የሚታወቁት ለአንድ ሰው ብቻ ነው—ለምሳሌ፣ ጌታ እራሱን “በዝግተኛ ትንሽ ድምጽ” (1 ነገሥት 19፥12) ለእናንተ በሚገልፅበት ጊዜ ማለት ነው።

ስለ ኤልያሳ ለበለጠ ማብራሪያ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ኤልይሳ” የሚለውን ርዕስ ይመልከቱ።

የጥናት ምልክት

በቤት እና በቤተክርስቲያን ለመማር የሚረዱ ሃሳቦች

1 ነገሥት 12:1–20

ክርስቶስን የሚመስሉ መሪዎች የሚመሩትን ሕዝብ ያገለግላሉ።

የሰለሞን ልጅ ንጉሥ ሮብዓም በ1 ነገሥት 12፡1-14 የሠራውን ስህተት እንዴት ትገልጻላችሁ? ሮብዓም መንግሥቱን እንዲያድን የረዱት የክርስቶስ ዓይነት ባሕርያት የትኞቹ ናቸው? (ቁጥር 7ማቴዎስ 20፡25–28ሞዛያ 2፡10–21 ተመልከቱ)። እነዚህን ባህሪያት እንደ መሪ—በቤተክርስቲያን ጥሪም ሆነ በራሣችሁ ህይወት እንዴት ልትጠቀሙባቸው ትችላላችሁ?

1 ነገስት 17:8–1619:19–21

የሴሚናሪ ምልክት
መስዋዕት ለማድረግ መጋበዝ እምነቴን በኢየሱስ ክርስቶስ lላይ እንድለማመድ እድል ነው።

ነቢዩ ኤልያስ አንዲት መበለት ራሷንና የተራበውን ልጇን ከመመገቧ በፊት ምግብና ውኃ እንድትሰጠው ጠየቃት። ለምን እንዲህ አደረገ? የኤልያስ ጥያቄ ለዚህ ትንሽ ቤተሰብ እንደበረከት ሊታይ ይችላል። የጌታ በረከት ያስፈልጋቸው ነበር፣ የጠንካራ እምነት በረከትን ጨምሮ መስዋዕትነት በረከቶችን ያመጣል።

1 ነገሥት 17፡8–16ን ስታነቡ፣ ይህችን መበለት እንደሆናችሁ አስቡ። ስለ እርሷ ምን ያስደንቃችኋል? እንዲሁም በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ መተማመንን የሚሹ ምርጫዎችን ዝርዝር ማውጣት ትችላላችሁ (ለምሳሌ፡ ለወጣቶች ጥንካሬ፡ ምርጫ ማድረግ መመሪያ [2022] ይመልከቱ)። እምነትን ስለመለማመድ ከዚህች መበለት ምን ትማራላችሁ?

1 ነገሥት 19፡19-21 ላይ ያለው የኤልሳዕ ድርጊት ከመበለቲቱ ድርጊት ጋር እንዴት ይመሳሰላል?

አዳኙን ለመከተል ስለከፈላችሁት መስዋዕትነቶች አስቡ። 1 ነገስት 17:8–1619፡19–21 ስለ እነዚህ መሥዋዕትነቶች ምን ያስተምራችኋል? አዳኙን ማወቃችሁ መስዋዕቶችን እንድትከፍሉ ሲጠይቃችሁ እንዴት ይረዳችኋል? የባረካችሁ እንዴት ነው?

በተጨማሪ ማቴዎስ 4:18–226:25–33ሉቃስ 4:24-26፤ “Elijah and the Widow of Zarephath” (ቪዲዮ)፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍት፤ “When Faith Endures,” መዝሙሮች፣ ቁ.128. ይመልከቱ።

10:13

Elijah and the Widow of Zarephath

1 ነገሥት 18

“እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ።”

እስራኤላውያን የማዕበልና የዝናብ አምላክ በመባል የሚታወቀውን በኣልን የሚያመልኩበት በቂ ምክንያት እንዳላቸው ሆኖ ተሰምቷቸው ሊሆን ይችላል። ከሦስት ዓመታት ድርቅ በኋላ ዝናብ አጥብቀው ፈለጉ። በኣልን ማምለክ ደግሞ በንጉሱና በንግሥቲቱ ዘንድ ተቀባይነት ያለውና የሚበረታታ ነበር። 1 ነገሥት 18ን በምታነቡበት ጊዜ፣ በዘመናችን አንድ ሰው ጌታን ለመከተል ቁርጠኛ ለምን ላይሆን እንደሚችል አስቡ። በዚህ ምእራፍ ውስጥ ጌታ ስለራሱ ለማስተማር የሞከረው ምን ይመስላችኋል? አዳኙ ለመከተል የተሰጣችሁ እንድትሆኑ የረዷችሁ ልምዶች ምንድናቸው?

እንዲሁም ዲ ቶድ ክርስቶፈርሰን፣ “Choice and Commitment” (ዓለም አቀፍ የወጣቶች ሃይማኖታዊ ጉባኤ፣ ጥር. 12፣ 2020 (እ.አ.አ))፣ የወንጌል ላይብረሪ ይመልከቱ።

ኤልያስ በኮሬብ ተራራ ላይ

የኤልያስ ምስል፣ በዊልሰን ኦንግ

1 ነገሥት 19፥1–18

ጌታ በብዛት በጸጥተኛና ቀላል መንገዶች ይናገራል።

በሚያሳዝን ሁኔታ፣ በቀርሜሎስ ተራራ ላይ የተደረገው ተአምር የኤልያስን ተልእኮ ቀላል አላደረገውም። እንደውም ህይወቱ አደጋ ላይ ስለወደቀ በበረሃ ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ መደበቅ ነበረበት። እዚያ፣ በብቸኝነት እና ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ሳለ፣ ከጌታ ጋር በቀርሜሎስ ተራራ ከነበረው ልምድ የተለየ ነገር ገጠመው። በ1 ነገሥት 19፥1–18 ያለው የኤልያስ ተሞክሮ በችግራችሁ ጊዜ ጌታ እንዴት እንደሚገናኛችሁ ምን ያስተምራችኋል?

ጌታ እንደተናገራችሁ ስለተሰማችሁ ጊዜ አሰላስሉ። ከእናንተ ጋር የሚገናኝበትን መንገድ እንዴት ትገልጹታላችሁ? “ትንሽ” እና “የዝምታ ድምጽ” የሚሉት ቃላት የመንፈስን ድምጽ ለመግለጽ ጥሩ መንገዶች የሆኑት ለምንድን ነው? ከሔለማን 5፡30ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 6፡22–2311፡12–14 ሌላ ምን ቃል ታገኛላችሁ? የጌታን መመሪያ በብዛት ለመቀበል ምን ማድረግ ይጠበቅባችኋል?

በተጨማሪ መዝሙር 46፡10 ይመልከቱ።

ትምህርትን ለማሻሻል ብዙ የስሜት ህዋሳትን ተጠቀሙ። ሁላችንም ስለ አለም የምንማረው በአምስቱ የስሜት ህዋሳቶቻችን ነው። እነዚያን የስሜት ህዋሳት መጠቀም የወንጌል ትምህርትን ሊያሳድግ ይችላል። ለምሳሌ፣ በ1 ነገሥት 19 ውስጥ ስለ ጌታ ድምጽ ስትማሩ ወይም ስታስተምሩ “ትንሽ” እና “የዝምታ ድምጽ” የሚሉትን ቃላት ለማሳየት ልትጠቀሙባቸው ስለምትችሏቸው ምስሎች ወይም ድምፆች አስቡ።

ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የሊያሆና እና የለወጣቶች ጥንካሬ መጽሔቶች ዕትሞችን ይመልከቱ።

የልጆች ክፍል ምልክት 

ልጆችን ለማስተማር የሚረዱ ሀሳቦች

1 ነገሥት 17

በእርሱ ላይ እምነት ሲኖረኝ ጌታ ይባርከኛል።

  • ልጆቻችሁ በ1 ነገሥት 17 ላይ ያለውን የእምነት ታሪኮች እንዲማሩ ለመርዳት፣ እንደ ወፎች፣ ዳቦ ወይም ወንድ ልጅ ያሉ ሥዕሎች ወይም ቁሳቁሶች በመጠቀም ታሪኮቹን ማሳየት ትችላላችሁ። እነዚህን ታሪኮች ለልጆቻችሁ ስትነግሩ ከእያንዳንዱ ታሪክ ጋር የሚሄደውን ምስል ወይም ቁሳቁስ እንዲያገኙ ጋብዟቸው። “ነቢዩ ኤልያስ” (በየብሉይ ኪዳን ታሪኮች፣ 121–24) እነዚህን ታሪኮች ለመንገር ሊረዳችሁ ይችላል። በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እምነት ስለማሳየት እያንዳንዱ ታሪክ ምን ያስተምረናል?

    1:58

    Elijah the Prophet

  • ልጆቻችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያላቸውን እምነት የሚያሳዩባቸውን መንገዶች እንዲያስቡ እርዷቸው። እንደ “I Have Faith in the Lord, Jesus Christ” (የወንጌል ላይብረሪ) የመሰለን ስለ እምነት የሚገልጽ መዝሙር አብራችሁ ዘምሩ እንዲሁም ከመዝሙሩ ስለ እምነት የተማራችሁትን ለሌሎች አካፍሉ።

ኤልያስ፣ አንዲት መበለት እና ልጇ

የኤልያስ ምሳሌ እና የመበለቲቱ ልጅ መፈወስ ስዕል፣ በቻርለስ ኤድመንድ ብሩክ

1 ነገሥት 17፡8–16

ጌታ እንድሰዋ ሲጠይቀኝ በእምነት መታዘዝ እችላለሁ።

  • ልጆቻችሁ ጌታ መበለቲቱ ለኤልያስ እንድትሰጥ የጠየቃትን (1 ነገሥት 17፡12–13 ተመልከቱ) መበለቲቱ ደግሞ በምላሹ ያገኘችውን ስዕል መሳል ይችላሉ (1 ነገሥት 17፡15–16 ተመልከቱ)። (በተጨማሪም የዚህን ሳምንት የአክቲቪቲ ገጽ ይመልከቱ።) እንዲሁም ለተሻለ ነገር የሚፈልጉትን ነገር የተዉ ሌሎች ሰዎችን ምስል መፈለግ ይችላሉ። ልጆቻችሁን የወንጌል አርት መጽሐፍ ወይም ኑ፣ ተከተሉኝ ውስጥ ሥዕሎችን እንዲፈልጉ ጋብዟቸው። ጌታ እንድንሠዋ የሚጠይቀን ምንድን ነው? የሚባርከን እንዴት ነው?

1 ነገሥት 18:17–39

ኢየሱስ ክርስቶስን ለመከተል መምረጥ እችላለሁ።

  • 1 ነገሥት 18፡17–39ን አንድ ላይ ስታነቡ፣ ልጆቻችሁ አንድ ጥቅስ መምረጥ እና የሚገልጸውን ነገር መሳል ይችላሉ። ታሪኩን በራሳቸው አንደበት ለመንገር ስዕሎቻቸውን መጠቀም ይችላሉ። (በተጨማሪም “ኤልያስ እና የበኣል ካህናት”ን በየብሉይ ኪዳን ታሪኮች፣ 125–28 ይመልከቱ።)

    2:17

    Elijah and the Priests of Baal

  • ልጆቻችሁ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመከተል ወይም ላለመከተል መወሰን ሊያስፈልጋቸው የሚችሉ ሁኔታዎች እንዲያስቡ እርዷቸው። ትክክለኛውን ምርጫ ሲያደርጉ የሚያሳይ የራሳቸውን ስዕል መሳል ይችላሉ። ኢየሱስን ለመከተል ለምን እንደመረጣችሁ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ።

1 ነገሥት 19፡9–12

ጌታ በመንፈስ ቅዱስ ትንሽ የጸጥታ ድምጽ ይናገረኛል።

  • 1 ነገሥት 19፡9–12ን ስታጠቃልሉ፣ ልጆቻችሁ ኃይለኛውን ነፋስ፣ የመሬት መንቀጥቀጥን እና እሳቱን የሚወክሉ ድርጊቶችን እንዲያሳዩ ጋብዟቸው። ከዚያም ዝም ብለው እንዲቀመጡ ጋብዟቸውና አብራችሁ ዝግ ባለ ድምጽ፣ “ከእሳቱ በኋላ ትንሽ የዝምታ ድምፅ” (ቁጥር 12) በአንድነት በሉ። (በተጨማሪም “ጌታ ለኤልያስ ተናገረ”፣ በየብሉይ ኪዳን ታሪኮች፣ 129-31 ይመልከቱ)። የመንፈስ ቅዱስ ትንሽ የዝምታ ድምጽ ስላጋጠማችሁ ጊዜ ለልጆቻችሁ ንገሩ።

    1:48

    The Lord Speaks to Elijah

  • እንደ “The Still Small Voice” (የልጆች የመዝሙር መጽሐፍ፣ 106–7) አይነት ስለ መንፈስ ቅዱስ የተዘመረ መዝሙር በዝግታ ዘምሩ። መንፈስን እንዳንገነዘብ ምን ሊያዘናጋን ይችላል? እሱን እንድንሰማው ምን ሊረዳን ይችላል?

ተጨማሪ ሃሳቦችን ለማግኘት የዚህን ወር የጓደኛ መጽሔት ዕትም ይመልከቱ።

የሰራፕታዋ መበለት እና ልጅዋ

የሰራፕታ መበለት፣፣ በሮዝ ዳቶክ ዳል

የልጆች የአክቲቪቲ ገጽ፡- ጌታ እንድሰዋ ሲጠይቀኝ በእምነት መታዘዝ እችላለሁ