2020–2024
የከበረ የብኩርና መብት ያላችሁ ወጣቶች ሆይ
የጥቅምት 2024 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


12:32

የከበረ የብኩርና መብት ያላችሁ ወጣቶች ሆይ

ልጆቹን በደህና ወደ እርሱ በማምጣት ስራው እንድትረዱ፣ እግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ልጆች እናንተን ያምናል።

ሽማግሌ ስቲቭንሰን፣ ይህ መቼም የማይረሳ ጉባኤ ነው።

ቤተሰባችን Children’s Letters to God [ለእግዚአብሔር የተፃፉ የልጆች ደብዳቤዎች]የተባለች ትንሽ መጽሐፍ ሁልጊዜ በማንበብ ይደሰት ነበር። የተወሰኑት ቀርበውላችሁሃል፦

“አምላክ ሆይ፣ ሰዎች እንዲሞቱ ከመፍቀድና አዲስ ከመፍጠር ይልቅ፣ ለምን አሁን ያሉትን ብቻ አታስቀምጥም?”

“እንዴት አስር ህጎች ብቻ ኖሩህ፣ የእኛ ትምህርት ቤት ግን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አሉት?”

“ቶንሲልን መልሰህ የምታወጣው ከሆነ ለምን አስገባኸው?”

ዛሬ ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ጊዜ የለም፤ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ከወጣቶች ለምሰማው ሌላ ጥያቄ መልስ መስጠት እፈልጋለሁ። ከኡላንባታር፣ ሞንጎሊያ፣ ለቶማስ፣ ኢይዳሆ ድረስ፣ ጥያቄው ተመሣሣይ ነው፦ “ለምን? ለምንድነው የኋለኛው ቀን ቅዱሳን ከሌሎች በተለየ ሁኔታ መኖር ያለባቸው?”

የተለየ መሆን ከባድ እንደሆነ አውቃለሁ—በተለይ ወጣት ከሆንክ እና ሌሎች ሰዎች እንዲወዱህ በጣም የምትፈልግ ከሆነ። ሁሉም ሰው መስማማት ይፈልጋል፣ እናም ይህ ፍላጎት በማህበራዊ ሚዲያ እና በሳይበር ጉልበተኝነት በተሞላው በዛሬው ዲጂታል አለም ጤናማ ባልሆነ መጠን ጎልቶ ይታያል።

ስለዚህ በዛ ሁሉ ጫና የኋለኛው ቀን ቅዱሳን በተለየ ሁኔታ የሚኖሩት ለምንድን ነው? ብዙ ጥሩ መልሶች አሉ፦ የእግዚአብሔር ልጆች ስለሆናችሁ። ለመጨረሻው ቀናት ተጠብቃችሁ ስለቆያችሁ። የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ስለሆናችሁ።

ሆኖም እነዚያ መልሶች ሁል ጊዜ እናንተን የሚለዩዋችሁ አይደሉም። ሁሉም የእግዚአብሔር ልጅ ነው። አሁን በምድር ላይ ያለ ሁሉ በኋለኛው ቀናት ወደዚህ ተልኳል። ነገር ግን ሁሉም ሰው እናንተ እንደምትጥሩት የጥበብን ቃል ወይም የንጽሕና ህግን አይኖሩም። የዚህ ቤተክርስቲያን አባላት ያልሆኑ ብዙ ጀግኖች የክርስቶስ ደቀመዛሙርት አሉ። ነገር ግን እንደ እናንተ በሚስዮን አያገለግሉም እንዲሁም ቅድመ አያቶቻቸውን ወክለው በጌታ ቤት ውስጥ ሥርዓቶችን አያከናውኑም። የበለጠ መኖር አለበት፣ ደግሞም አለ።

ዛሬ በሕይወቴ ውስጥ ትርጉም ያለው ተጨማሪ ምክንያት ላይ ማተኮር እፈልጋለሁ። በ1988 (እ.አ.አ)፣ ራስል ኤም. ኔልሰን የተባለ ወጣት ሐዋርያ በብሪገም ያንግ ዩኒቨርሲቲ “ለቃል ኪዳኑ አመሰግናለሁ” የሚል ንግግር አድርጎ ነበር። በውስጡ፣ በዚያን ጊዜ ሽማግሌ ኔልሰን የስነምግባር ነጻ ምርጫችንን ስንጠቀም እና ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳኖችን ስንገባ እንዲሁም ስንጠብቅ፣ እግዚአብሔር በየዘመኑ ከቅድመ አያቶቻችን ጋር የገባውን የዘለአለም ቃል ኪዳን ወራሾች እንደምንሆን ገለጹ። በሌላ አነጋገር፣ “የቃል ኪዳን ልጆች” እንሆናለን። ያ የተለየን ያደርገናል። ያ የብኩርና መብትን ጨምሮ አያቶቻችን የተቀበሉትን እነዚያኑ በረከቶች እንድናገኝ ያደርገናል።

የብኵርና መብት! ያንን ቃል ሰምታችሁ ይሆናል። ስለ እሱ መዝሙሮችን እንኳን እንዘምራለን፦ “የከበረ የብኩርና መብት ያላችሁ ወጣቶች ሆይ፣ ቀጥሉ፣ ቀጥሉ፣ ቀጥሉ!” ትኩረትን የሚስብ ቃል ነው። ግን ምን ማለት ነው?

በብሉይ ኪዳን ዘመን አባት ከሞተ፣ የበኩር ልጁ እናቱን እና እህቶቹን የመንከባከብ ሀላፊነት ነበረበት። ወንድሞቹ ርስታቸውን ተቀብለው ራሳቸውን ችለው ለመኖር በየፊናቸው ሄዱ፣ የብኩርና ልጅ ግን የትም አልሄደም። እሱ አግብቶ የራሱ ቤተሰብ ይኖረዋል፣ ነገር ግን የአባቱን ቤት ጉዳዮች ለማስተዳደር እስከ ዘመኑ ፍጻሜ ድረስ እዛው ይቆያል። በዚህ ተጨማሪ ኃላፊነት ምክንያት፣ በውርሱ ላይ ተጨማሪ ተሰጠው። ሌሎችን መምራት እና መንከባከብ ብዙ የሚጠይቅበት ነበርን? የተሰጠውን ተጨማሪ ውርስ ሲታሰብ፣ ብዙ አይደለም።

ዛሬ ስለምድራዊ ቤተሰባችሁ የውልደት ቅደም ተከተል ወይም ስለብሉይ ኪዳን የሥርዓተ-ፆታ ሚናዎች እየተነጋገርን አይደለም። ከክርስቶስ እና በሠማይ ካለው አባታችሁ ጋር ለመግባት በመረጣችሁት የቃል ኪዳን ግንኙነት ምክንያት ከክርስቶስ ጋር እንደ አጋር ወራሽ ስለምትቀበሉት ርስት እየተነጋገርን ነው። እግዚአብሔር ከሌሎች ልጆቹ በተሻለ መንገድ እንድትመሯቸው እና እንድታገለግሏቸው የሚጠብቅባችሁ በጣም ብዙ ነው? የተሰጧችሁን —ሥጋዊ እና መንፈሳዊ በረከቶች—ስታስቡ፣ ብዙ አይደለም።

የብኩርና መብት ስላላችሁ ከሌሎች ትበልጣላችሁ ማለት ነውን? አይደለም፣ ነገር ግን ሌሎች የተሻሉ እንዲሆኑ መርዳት ይጠበቅባችኋል ማለት ነው። ብኩርናችሁ የተመረጣችሁ ናችሁ ማለት ነውን? አዎ፣ ነገር ግን ሌሎችን ለመግዛት አይደለም፤ እነርሱን ለማገልገል ነው የተመረጣችሁት። የብኩርና መብታችሁ የእግዚአብሔር ፍቅር ማስረጃ ነውን? አዎ፣ ነገር ግን ከሁሉም በላይ አስፈላጊ የሆነው፣ እምነት እንደጣለባችሁ ማረጋገጫ መሆኑ ነው።

መወደድ አንድ ነገር ነው እንዲሁም መታመን ሙሉ በሙሉ ሌላ ነገር ነው። በለወጣቶች ጥንካሬ መመሪያ ውስጥ እንዲህ እናነባለን፦ “የሰማይ አባታችሁ ይተማመንባችኋል። የወንጌልን ሙላት እና ከእርሱ ጋር የሚያስተሳስሩ እና ኃይሉን ወደ ህይወታችሁ የሚያመጡትን የተቀደሱ ስርአቶችን እና ቃል ኪዳኖችን ጨምሮ ታላቅ በረከቶችን ሰጥቷችኋል። በእነዚያ በረከቶች ተጨማሪ ኃላፊነት ይመጣል። በአለም ላይ ለውጥ ማምጣት እንደምትችሉ ያውቃል ይህ ደግሞ በብዙ ሁኔታዎች ከአለም የተለዩ መሆንን ይጠይቃል።”

ምድራዊ ተሞክሯችን እግዚአብሔር ልጆቹን ከአንዱ የባህር ዳርቻ ወደ ሌላው ሲጓዙ ከላከበት የመርከብ ጋር ሊመሳሰል ይችላል። ጉዞው ለመማር፣ ለማደግ፣ ለመደሰት እና ለመሻሻል በሚያስችሉ እድሎች የተሞላ ነው፣ ነገር ግን በአደጋዎች የተሞላም ነው። እግዚአብሔር ሁሉንም ልጆቹን ይወዳል እንዲሁም ስለ ደህንነታቸው ያስባል። አንዳቸውንም ማጣት አይፈልግም፣ ስለዚህ ፈቃደኛ የሆኑትን የእሱ ቡድን አባላት እንዲሆኑ ይጋብዛል —እነርሱም እናንተ ናችሁ። ቃል ኪዳኖችን ለመፈጸም እና ለማክበር ስለመረጣችሁ፣ እምነቱን ለእናንተ ሰጥቷችኋል። እናንተ ልዩ፣ ለውጥ ያላችሁ፣ እና የተገነጠፋችሁ እንድትሆኑ ያምናችኋል፣ ይህም እንደምትሠሩት ባመነባችሁ በጣም አስፈላጊ በሆነው ሥራ ምክንያት ነው።

ስለ እርሱ አስቡ! በምድር ላይ ካሉት ሰዎች ሁሉ፣ ልጆቹን በደህና ወደ እርሱ በማምጣት ስራው እንድትረዱ፣ የቃል ኪዳኑ ልጆች—የእሱ ቡድን አባላት—እግዚአብሔር እናንተን ያምናል። ፕሬዚዳንት ብሪገም ያንግ በአንድ ወቅት፣ “በሰማይ ያሉት መላእክቶች ይህንን ትንሽ እፍኝ የሆኑ ሰዎችን ይመለከታሉ” ማለታቸው ምንም አያስደንቅም።

ምድር እየተባለ የሚጠራውን የዚህን መርከብ ዙሪያ ገባ ስትመለከቱ፣ ሌሎች ሰዎች በቡና ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ሲጠጡ፣ በካሲኖዎች ውስጥ ቁማር ሲጫወቱ፣ ገላን በጣም የሚያሣይ ልብስ ለብሰው፣ በሞባይል ስልካቸው ያለማቋረጥ ወደ ላይ እና ወደ ታች ሲያደር እና የኤሌክትሮኒክ ጨዋታዎችን በመጫወት ብዙ ጊዜ ሲያባክኑ ታያላችሁ። ግን “ለምንድን ነው ያንን እኔ ማድረግ የማልችለው?፣” ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ። እናንተ ተራ ተሳፋሪ እንዳልሆናችሁ ማስታወስ ትችላላችሁ። እናንተ የመርከቡ ሠራተኞች አባል ናችሁ። ተሳፋሪዎች የሌሉባቸው ኃላፊነቶች አሉባችሁ። እህት አርዴት ካፕ በአንድ ወቅት እንደተናገረችው፣ “በባህር ዳርቻ ላይ እንዳሉ እንደሌሎች ዋናተኞች የምትመስሉ ከሆነ ህይወት[ጠባቂ] መሆን አትችሉም።

እናም በሁሉም ተጨማሪ ግዴታዎች ተስፋ ከመቁረጣችሁ በፊት፣ እባካችሁ የመርከቡ ሠራተኞች አባላት ሌሎቹ ተሳፋሪዎች የማይቀበሉትን ካሣ እንደሚቀበሉ አስታውሱ። ሽማግሌ ኒልኤል. አንደርሰን እንዳሉት፣ “ለጻድቃን የማካካሻ መንፈሳዊ ኃይል አለ፣” “ታላቅ ማረጋገጫ፣ የበለጠ ማረጋገጫ እና የበለጠ መተማመን።” እንደ ጥንቱ አብርሃም፣ የበለጠ ደስታና ሰላም፣ ታላቅ ጽድቅ እና የላቀ እውቀት ታገኛላችሁ። ማካካሻችሁ የሰማይ ቤት እና በወርቅ የተነጠፉ ጎዳናዎች ብቻ አይደሉም። የሰማይ አባት ያለውን ሁሉ በቀላሉ ቢሰጣችሁ ቀላል ይሆን ነበር። የእርሱ ዓላማ እርሱ የሆነውን ሁሉ እንድትሆኑ መርዳት ነው። ስለዚህ፣ ቃል ኪዳኖቻችሁ ከናንተ የበለጠ ይፈልጋሉ፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሙሉ አቅማችሁ ላይ እንድትደርሱ እያደረገ ያለው እንደዚያ ነው።

ይህም “ለምንም ለመጠየቅ የበዛ ነው፣ ነገር ግን እናንተ ምንም አይደላችሁም!” እናንተ የክበ ብኩርና ወጣቶች ናችሁ። ከእግዚአብሔር እና ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያላችሁ የቃል ኪዳን ግንኙነት የፍቅር እና የመተማመን ግንኙነት ነው፣ በዚህም የእነርሱን ፀጋ፣ እንዲሁም የእነሱን መለኮታዊ እርዳታ፣ የጥንካሬ ስጦታ እና የማስቻል ሃይልን የበለጠ ልታገኙበት ትችላላችሁ። ያ ኃይል እንዲያው ዝም ብሎ የምኞት አስተሳሰብ፣ እድል አምጪ ወይም የተጠበቀውን የሚፈጽም ትንቢት አይደለም። ይህ እውነትነው።

የብኩርና ኃላፊነታችሁን ስትወጡ፣ መቼም ብቻችሁን አትሆኑም። የወይኑ ቦታ ጌታ ከእናንተ ጋር ይሰራል። ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዛችሁ እየሠራችሁ ነው። በእያንዳንዱ አዲስ ቃል ኪዳን —እና ከእሱ ጋር ያለችሁን ግንኙነት እየጠነከረ ሲሄድ —አንድ ላይ እስክትገናኙ ድረስ እርስ በርሳችሁ እያጠበቃችሁ እያጠበቃችሁ ትያያዛላችሁ። በዚያ ቅዱስ የጸጋው ምልክት ውስጥ፣ ከአለም በተለየ መልኩ ልክ አዳኙ በኖረበት መንገድ ለመኖር ፍላጎት እና ጥንካሬን ታገኛላችሁ። ኢየሱስ ክርስቶስ ስላገኛችሁ ይህንን አግኝታችኋል!

2 ኔፊ 2፥6 ላይ፣ “ስለዚህ፣ ቤዛነት በቅዱሱ መሲህ እና በእርሱ አማካይነት ይመጣል፤ ምክንያቱም እርሱ በፀጋና በእውነት የተሞላ ነው” የሚል እናነባለን። እርሱ በእውነት የተሞላ ስለሆነ፣ እናንተን በትክክል ያያችኋል— ጉድለቶችን፣ ድክመቶችን፣ ጸጸቶችን እና ሁሉንም። እርሱ ጸጋ የተሞላ ስለሆነ፣ ልትሆኑ እንደምትችሉት ያያችኋል። ባለችሁበት ያገኝችኋል እንዲሁም ንስሀ እንድትገቡ እና እንድትሻሻሉ፣ እንድታሸንፉ እና እንድትሆኑ ይረዳችኋል።

“የከበረ የብኩርና መብት ያላችሁ ወጣቶች ሆይ፣ ቀጥሉ፣ ቀጥሉ፣ ቀጥሉ!” ዛሬ፣ ከ20 አመታት በኋላም እና ለዘለአለም እንደምትወደዱ እና እንደምትታመኑ እመሰክራለሁ። ብኩርናችሁን ለማይረባ የምሥር ወጥ አትሸጡ። ሁሉንም ነገር በከንቱ አትቀይሩ። የተወለዳችሁት ዓለምን ለመለወጥ ሆኖ ሳለ ዓለም እንዲለውጣችሁ አትፍቀዱ። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።

ማስታወሻዎች

  1. በስቱዋርት ሃምፕል እና ኤሪክ ማርሻል፣ Children’s Letters to God [1991 (እ.አ.አ)]።

  2. ረስልኤም. ኔልሰን፣ “Thanks for the Covenant” [Brigham Young University devotional, ህዳር 22፣ 1988 (እ.አ.አ)]፣ 4፣ speeches.byu.edu ይመልከቱ።

  3. 3 ኔፊ 20፥26፤ እንዲሁም ረስልኤም. ኔልሰን፣ “Choices for Eternity” [አለማቀፍ የወጣቶች መንፈሳዊ ስብሰባ፣ ግንቦት 15፣ 2022 (እ.አ.አ)]፣ የወንጌል ላይብረሪ፤ ረስልኤም. ኔልሰን፣ “Children of the Covenant፣” ኢንሳይን፣ ግንቦት 1995 (እ.አ.አ)፣ 32–35።

  4. 3 ኔፊ 20፥25 ተመልከቱ፤ በተጨማሪም የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ “የአብርሃም፣ ቃል ኪዳን ተመልከቱ፤ በተጨማሪም አብርሃም 2፥6 (የተስፋይቱ ምድር፥ የሰለስቲያል ክብር፣ ዘላለማዊ ቤተሰቦች)፣ ዘፍጥረት 13፥16ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 132፥30–31 (ትውልድ፥ ዘላለማዊ ጭማሪ)፣ እና አብርሃም 1፥182፥11 ተመልከቱ (ክህነት፥ ስልጣን፣ ቁልፎች፣ ስነስርዓቶች፣ ቃል ኪዳኖች እና መለኮታዊ ሃይል፤ እንዲሁም ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “በክህነት ቁልፎች ስጦታ ደስ ይበላችሁ፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2024 (እ.አ.እ)፣ ገጽ 119–23 ይተመልከቱ።)

  5. “Carry On,” መዝሙር፣ ቁጥር. 255

  6. ራስልኤም. ኔልሰንን፣ “Youth of the Noble Birthright፥ What Will you Choose?” ይመልከቱ። (ለወጣት ጎልማሶች የቤተክርስቲያን አምልኮ ሥርዓት፣ መስከረም 6፣ 2013(እ.አ.አ))፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍት፤ እንዲሁም ራስል ኤም. ኔልሰንን፣ “ለቃል ኪዳኑ አመሰግናለሁ፣” peeches.byu.edu፤ የመጻህፍት ምሪት፣ “የበኩር ልጅ፣” የወንጌል ቤተ መጻሕፍት ይመልከቱ ።

  7. ሉቃስ 12፥4217፥7–10ን ይመልከቱ።

  8. ሮሜ 8፥17፣ በተጨማሪም ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 76፥54–5588፥107ን ተመልከቱ።

  9. ጌታ እንዲህ አለ፣ “እጅግ ቀላል ነገር ነው”(1 ኔፊ 21፥6)።

  10. 1 ጴጥሮስ 2፥9ተመልከቱ።

  11. ጌታ እንዲህ አለ፣ “እስራኤል ሆይ አንተ አሸከሬ ነህ” (1 ኔፊ 21፥3)።

  12. ዘጸአት 2፥25ተመለከቱ።

  13. ለወጣቶች ጥንካሬ፥ ምርጫ የማድረግ መመሪያ (2022 (እ.አ.አ))፣ 4፤ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 84፥18–25107፥18–21፣ ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “Youth of the Noble Birthright፥ What Will you Choose?” ይመልከቱ።

  14. ትምህርት እና ቃል ኪዳን 20፥77 ተመልከቱ።

  15. 1 ጴጥሮስ 2፥9 ተመልከቱ።

  16. ሙሴ 1፥6፣ እንዲሁም “የአሮናዊ ክህነት ቡድን ጭብጥ”፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍትን ይመልከቱ።

  17. የቤተክርስቲያኗ ፕሬዘዳንቶች ትምህርቶች፤ ብሬገም ያንግ (1997 እ.አ.አ)፣ 309።

  18. አርዴት ግሪን ካፕ ፣ I Walk by Faith (1987 እ.ኤ.አ)፣ ገጽ 97።

  19. ሞዛያ 2፥22፣ 41ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 59፥23 ተመልከቱ።

  20. ኒልኤል. አንደርሰን፣ “A Compensatory Spiritual Power for the Righteous” (Brigham Young University devotional, ነሐሴ፣ 18, 2015 እ.ኤ.አ)፣ speeches.byu.edu.

  21. አብርሐም 1፥2 ተመልከቱ።

  22. ዳልን ኤች. ኦክስ፣ “With Full Purpose of Heart,” (2002 እ.አ.አ) ገጽ 38ን ተመልከቱ።

  23. ኬኔት ኮፕ፣ “The Best for Last,” Voices (አልበም 1991 እ.አ.አ)።

  24. አልማ 53፥2057፥27 ተመልከቱ።

  25. ዲይተር ኤፍ. ኡክዶርፍ፣ “የጸጋ ስጦታ፣” ሊያሆና፥ ግንቦት 2015 (እ.አ.አ)፣ ገጽ 107)፤ በተጨማሪም የመጻህፍት መምሪያ፣ “ጸጋ” የወንጌል ቤተመጽሐፍት ይመልከቱ። በቅዱሳት መጻህፍት ውስጥ በተገኙት ብዙ የእግዚአብሔር ኃይል መግለጫዎች ግራ ይጋቡኝ ነበር። ጸጋን እንደ ኃይል እንደሚያስችል ይናገራሉ ፊልጵስዮስ 4፥13ግን ደግሞ የክርስቶስ ብርሃን እንደ ኃይል ነው (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 88፥13) ይመልከቱ። የእምነትን ኃይል እናነባለን አልማ 18፥35፣ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሞሮኒ 10፥7፣ እና ከላይ የመጣ ሀይል በቤተመቅደስ ውስጥ ቃል የተገባለት ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 38፥32105፥11 ተመልከቱ። ቅዱሳት መጻሕፍት ስለ ክህነት ኃይልም ያስተምራሉ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 113፥8፣ ተመልከቱ። … አንደኛው የት እንዳበቃ እና ሌሎቹ እንደጀመሩ ማወቅ አልቻልኩም። በመጨረሻ፣ ‘ከእግዚአብሔር ኃይል በቀር ሌላ ኃይል እንደሌለ’ ተገነዘብኩ” (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 8፥7፤ እንዲሁም ሮሜ 13፥1 ተመልከቱ)። የእግዚአብሔር ኃይል የተለያዩ መለያዎች የተለያዩ ኃይላትን አይገልጹም፣ ነገር ግን የተለያየ መጠን፣ አጠቃቀም እና የአንድ ኃይል ገጽታዎች።

  26. ያዕቆብ 5፥72 ተመልከቱ።

  27. ያዕቆብ 6፥5 ተመልከቱ።

  28. 3 ኔፊ 22፥17 ተመልከቱ።

  29. መዝሙሮች፣ ቁጥር 255።

  30. ዘፍጥረት 25፥29–34 ተመልከቱ።

  31. 3 ኔፊ 20፥38፤ እንዲሁም ኢሳይያስ 55፥2 ተመልከቱ።