“የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች—ለወላጆች እና ጥሪ ለተሰጣቸው አስተማሪዎች፣” በአዳኝ መንገድ ማስተማር፦ በቤት እና በቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚያስተምሩ ሁሉ [2022 (እ.አ.አ)]
‘’የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች፣’’ በአዳኙ መንገድ ማስተማር
የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች—ለወላጆች እና ጥሪ ለተሰጣቸው አስተማሪዎች
እያንዳንዱ አጥቢያ አስተማሪዎች ስለክርስቶስ መሰል አስተምህሮት መርሆዎች በጋራ የሚመካከሩበት የሩብ ዓመት የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎችን ማካሄድ አለበት። በእነዚህ ስብሰባዎች ውስጥ፣ ወላጆች እና ሌሎች አስተማሪዎች ስለ ክርስቶስን መሰል አስተምህሮት መርሆች በጋራ መወያየት ይችላሉ (አጠቃላይ መመሪያ መፅሐፍ፦ በኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል፣ 13.4፣ 13.5፣ 17.4፣ 17.5፣ የወንጌል ቤተመጻህፍትን ተመልከቱ)።
የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች የሚካሄዱት በየሩብ አመቱ እሁድ በ50 ደቂቃዎቹ የትምህርት ጊዜ ወቅት ነው።
ለወላጆች የሚካሄዱ የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች
እነዚህን ስብሰባዎች የሚመራው ማን ነው? አብዛኛውን ጊዜ፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አመራር አባል ለወላጆች የሚካሄዱትን የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች ይመራል። ይሁን እንጂ፣ የኤጲስ ቆጶስ አመራር ሌላ የአጥቢያው አባላት ስብሰባዎችን አልፎ አልፎ እንዲመሩ ሊመድብ ይችላል።
የአጥቢያው ሸንጎ፣ በሰንበት ትምህርት ቤት አመራር እርዳታ፣ ለወላጆች የሚካሄዱትን የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች ይቆጣጠራል። በጋራ ለወላጆች እና ለቤተሰቦች አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ይመካከራሉ፣ እና በጌታ መንገድ ማስተማር ውስጥ ከሚገኙት የትኞቹ መርሆች ለፍላጎቶቻቸው ተስማሚ እንደሆኑ ለመወሰን አብረው ይሰራሉ።
ማን በዚያ ስብሰባ መገኘት ይኖርበታ? የአጥቢያ ሸንጎ የተለዩ ወላጆችን ለመጋበዝ ወይም በስብሰባው መሳተፍ ለሚፈልጉት ሁሉ ክፍት ለማድረግ ይወስናል።
እነዚህ ስብሰባዎች መካሄድ የሚኖርባቸው መቼ ነው? ለወላጆች የሚካሄዱ የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች፣ በአጥቢያ ሸንጎ እንደተወሰነው፣ በማንኛውም እሁድ ሊካሄዱ ይችላሉ።
ጥሪ ለተሰጣቸው አስተማሪዎች የሚካሄዱ የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች
እነዚህን ስብሰባዎች የሚመራው ማን ነው? አብዛኛውን ጊዜ የሰንበት ትምህርት ቤት አመራር አባል ጥሪ ለተሰጣቸው አስተማሪዎች የሚካሄዱትን የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች ይመራል። ይሁን እንጂ፣ የኤጲስ ቆጶስ አመራር ሌላ የአጥቢያው አባላት ስብሰባዎችን አልፎ አልፎ እንዲመሩ ሊመድብ ይችላል።
የአጥቢያው ሸንጎ፣ በሰንበት ትምህርት ቤት አመራር እርዳታ፣ ጥሪ ለተሰጣቸው አስተማሪዎች የሚካሄዱትን የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች ይመራል። በጋራ ለአስተማሪዎች እና ለተማሪዎች አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ይመካከራሉ፣ እና በጌታ መንገድ ማስተማር ውስጥ ከሚገኙት የትኞቹ መርሆች ለፍላጎቶቻቸው ተስማሚ እንደሆኑ ለመወሰን አብረው ይሰራሉ።
ማን በዚያ ስብሰባ መገኘት ይኖርበታ? በአጥቢያው ውስጥ የቡድን ወይም የክፍል ትምህርቶችን የሚያስተምር ማንኛውም ሰው በየአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች ሊሳተፍ ይገባዋል። የቡድን ወይም የአደረጃጀት አመራር አባላት እንዲሁ ይጋበዛሉ።
እነዚህ ስብሰባዎች መካሄድ የሚኖርባቸው መቼ ነው? አስተማሪዎች የራሳቸውን መደበኛ ክፍል በማያስተምሩበት በእሁድ ቀን በየአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች ይሳተፋሉ።
-
የክህነት ቡድን፣ የሴቶች መረዳጃ ማህበር እና የወጣት ሴቶች አስተማሪዎች፣ በአካባቢ መሪዎች እንደተወሰነው፣ በመጀመሪያው ወይም በሶስተኛው እሁድ ላይ መሳተፍ ይችላሉ።
-
የሰንበት ትምህርት ቤት አስተማሪዎች፣ በአካባቢ መሪዎች እንደተወሰነው፣ በሁለተኛው ወይም በአራተኛው እሁድ ላይ መሳተፍ ይችላሉ።
-
የመጀመሪያ ክፍል አስተማሪዎች፣ በአጥቢያ የመጀመሪያ ክፍል እና በሰንበት ትምህርት አመራሮች እንደተወሰነው፣ በማንኛውም እሁድ መሳተፍ ይችላሉ። ከተፈለገ፣ የመጀመሪያ ክፍል አስተማሪዎች ልጆችን ስለማስተማር የተለዩ ሁኔታዎች ለመማከር ከሌሎች አስተማሪዎች ተለይተው ለብቻቸው ለመሰብሰብ ይችላሉ። ይህም በ20 ደቂቃ የመዝሙር ሰዓት፣ መደበኛው የእሁድ ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት ወይም በኋላ ወይም በሳምንቱ ሌላ ቀን ውስጥ ሊካሄድ ይችላል። ሁሉም የመጀመሪያ ክፍል አስተማሪዎች በተመሳሳይ ሳምንት ውስጥ በመጀመሪያ ክፍል ክፍለ ጊዜዎች የማይሳተፉ እንዳይሆኑ ሲባል በየእሩብ ዓመቱ ከአንድ በላይ የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎች ሊካሄዱ ይችላሉ። (ማስታወሻ፦ እንደአስፈላጊነቱ፣ የመጀመሪያ ክፍል አመራሮች የመጀመሪያ ክፍል አስተማሪዎች የአስተማሪ የምክክር ስብሰባዎችን እንዲሳተፉ ለመፍቀድ ተተኪ አስተማሪዎችን ይመድባሉ፣ ክፍሎችን ያቀላቅላሉ ወይም የ ሌላ ሁኔታዎችን ያመቻቻሉ።)
የስብሰባዎች አቀራረብ
የአስተማሪዎች የምክክር ስብሰባዎች—ለወላጆች እና ጥሪ ለተሰጣቸው አስተማሪዎች—ይህንን አቀራረብ ይከተላሉ፤
-
አካፍሉ እንዲሁም በጋራ ተማከሩ (ለ20 ደቂቃዎች)። በቤታቸው ወይም በክፍሎቻቸው ውስጥ ወንጌልን በሚያስተምሩበት ጊዜ ምን በትክክል እንደሚሰራ እንዲያካፍሉ ወላጆችን ወይም አስተማሪዎችን ጋብዙ። እየገጠሟቸው ያሉትን ተግዳሮቶች ወይም ሊያሻሽሏቸው የሚፈልጓቸውን ነገሮች እንዲሁ ሊያካፍሉ ይችላሉ።
-
በጋራ ተማማሩ (ለ15ደቂቃዎች)። በአዳኙ መንገድ ማስተማር ውስጥ ከሚገኙት መርሆች አንዱን ከወላጆች ወይም ከአስተማሪዎች ጋር ተወያዩ። ለእነዚህ ውይይቶች ኑ፣ ተከተሉኝ እንደ ግብአት ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል።
-
አቅዱ እንዲሁም ጋብዙ (ለ10 ደቂቃዎች)። በስብሰባው ወቅት ምን እንደተማሩ እና ያንንም እንዴት ተግባራዊ እንደሚያደርጉ እንዲያካፍሉ ወላጆችን ወይም አስተማሪዎችን ጋብዙ።