2025
ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የትንሳኤ ተስፋ እና ቃልኪዳን
ሚያዝያ 2025 (እ.አ.አ)


“ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የፋሲካ ተስፋ እና ቃልኪዳን፣” ሊያሆና፣ ሚያዝያ 2025 (እ.አ.አ)።

ወርሀዊ የሊያሆና መልዕክት፣ ሚያዝያ 2025 (እ.አ.አ)

ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የፋሲካ ተስፋ እና ቃልኪዳን

በትንሳኤ ተስፋ እና ቃልኪዳን ኢየሱስ ክርስቶስ የልባችንን ናፍቆት ይሞላል እንዲሁም የነፍሳችንን ጥያቄዎች ይመልሳል።

የማያፈራ የዛፍ ቅርንጫፍ

ምስል በማይክል ደንፎርድ

እባካችሁ ይህን መልእክት በምታነቡበት ጊዜ ጸጥታ የሰፈነበት ጊዜ እና የተቀደሰ መንፈሳዊ ቦታን ለመፍጠር ሞክሩ።

ብዙ ጊዜ፣ ዓለማችን በጫጫታ፣ በማስመሰል እና በትዕቢት የተሞላች ናት። ነገር ግን ለራሳችን እና ለእግዚአብሔር ራሳችንን ስናጋልጥ፣ ግልጽ እና ታማኝ ስንሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ያለው የትንሳኤ ተስፋ እና ቃልኪዳን እውን ይሆናል። በእንደዚህ ዓይነት ጊዜያት፣ እንዲህ እንማጸናለን፡-

“የቤተሰቤን አባል፣ ጓደኛዬን፣ የምወደውን ሰው ዳግም እንዴት ማየት እችላለሁ?”

“በብዙ ጊዜያዊ በሆኑ ‘ራሴን እመርጣለሁ’ የተሰኙ ግንኙነቶች ባሉበት ዓለም ውስጥ፣ በዙሪያዬ ላሉት እና ለራሴ ከእግዚአብሄር ጋር ሰላም፣ ተስፋ እና ህብረት እንዴት ይሰማኛል፣ ይህን የትስ አገኛለሁ? (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 107፡19 ይመልከቱ)”

“ልወደው የምችለው ሰው አለ—እንዲሁም በእውነት ማን ሊወደኝ ይችላል? የቃል ኪዳን ግንኙነቶች እንደ ተረት ተረት ብቻ ሳይሆን ከሞት ገመድ በጠነከሩ እስራቶች በእውነት በደስታ ለዘላለም ሊቆዩ ይችላሉ?”

“ብዙ ህመም፣ ስቃይ እና ኢፍትሃዊነት ባለበት፣ በኢየሱስ ክርስቶስ እና ዳግም በተመለሰው ወንጌል እና ቤተክርስትያን ውስጥ ሰላምን፣ አንድነትን እና መግባባትን ለመፍጠር እንዴት አስተዋጽዖ ማድረግ እችላለሁ?”

በዚህ የትንሳኤ ወቅት፣ የኢየሱስ ክርስቶስን እና የተስፋ ቃሉን ምስክርነቴን አካፍላለሁ።

የቃል ኪዳን ቁርኝት ተስፋ እና ዓላማ

በሰማይ ያለው የዘላለም አባታችን፣ እግዚአብሔር፤ የተወደደ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ እና መንፈስ ቅዱስ በግል ለእኛ ቅርብ ናቸው። የእነርሱ ወሰን የሌለው እና ዘላለማዊ ብርሃን፣ ርህራሄ እና የማዳን ፍቅር በፍጥረት አላማ እና በህልውናችን ውስጥ የተሳሰሩ ናቸው (አልማ 30፡44ሙሴ 6፡62–63 ይመልከቱ)።

በመንግሥተ ሰማይ በቅድመ ምድር ጉባኤ ላይ፣ “የአጥቢያ ኮከቦች በአንድነት [ዘምረዋል]፣ የእግዚአብሔርም [ወንዶች] ልጆች [እና ሴቶች ልጆች] ሁሉ እልል [ብለዋል]” (ኢዮብ 38፡7)። ምርጫ መርጠናል። አሁን የምንጓዘው በእምነት ነው። በራሳችን ልምድ እርግጠኛ በማንሆንበት ምድራዊ ህይወት፣ ተስፋ በመቁረጥ እና በፈተናዎች መካከል የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል ውበት፣ ግልጽነት፣ ደስታ እና አላማ እናገኛለን።

እርግጠኛ ባልሆነ ሁኔታ ውስጥ ብቻችንን መቅበዘበዝ የለብንም። ከሰማይ ጋር መገናኘት፣ በቤተሰብ፣ በቅዱሳን ቤት እና በማህበረሰብ ውስጥ እምነት እና አንድነትን መገንባት እንዲሁም እውነተኛ፣ ነፃ፣ ትክክለኛ፣ ደስተኛ እራሳችንን በፈቃደኝነት እና በደስታ ለእግዚአብሔር ትእዛዛት የምንታዘዝ መሆን እንችላለን። የኃጢያት ክፍያ—አንድ መሆን—በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ይህንን ቃል ኪዳን ያመጣል።

እያቆጠቆጠ ያለ አበባ ያለው የዛፍ ቅርንጫፍ

የኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና ተልዕኮ ተስፋ

በእያንዳንዱ ቀን የትንሳኤ ተስፋ እና ቃልኪዳን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም በሆነው በምድራዊ አገልግሎቱ ወቅት ያካፈላቸውን በረከቶች እና ትምህርቶች ያጠቃልላል። አስቀድሞ በመጀመሪያ የተሾመው፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ በመሆን ተወልዷል (ያዕቆብ 4፡5አልማ 12፡33–34ሙሴ 5፥7፣ 9ይመልከቱ)። በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሞገስን እያገኘ በጥበብና በቁመት አድጓል (ሉቃስ 2፡52 ይመልከቱ)። የአባቱን ፈቃድ ለማድረግ ብቻ በመፈለግ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአትን ይቅር ብሏል፣ በ ሽታን ፈውሷል፣ ሙታንን አስነስቷል፣ እንዲሁም የታመሙትን እና ብቸኛ የሆኑትን አጽናንቷል።

አንድ ጊዜ 40 ቀን ከጾመ በኋላ፣ “የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፣ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ልባቸው የተሰበረውን እፈውስ ዘንድ፣ ለታሰሩትም መዳንን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፣ የተሰበሩትንም ነጻ አወጣ ዘንድ ልኮኛል” በማለት መስክሯል (ሉቃስ 4:18፣ በተጨማሪም ኢሳይያስ 61:1⁠ን ይመልከቱ)።

ያም እያንዳንዳችን ነን።

በጌታም እራት ወቅት፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጥቧል (ዮሐንስ 13፡4–8ይመልከቱ)። በጥንቱም ሆነ በአዲስ አለማት፣ “የህይወት ውሃ” እና “የህይወት እንጀራ” የሆነው እርሱ ቅዱስ ቁርባንን አቋቁሟል። በተቀደሰው የቁርባን ስርአት፣ አብን በመጥራት የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በላያችን ላይ ለመውሰድ፣ ሁል ጊዜ እሱን ለማስታወስ እና ትእዛዛቱን እንድንጠብቅ መንፈሱ ሁል ጊዜ ከእኛ ጋር እንዲሆን ቃል እንገባለን (ሉቃስ 22፡19–203 ኔፊ 18፡7፣ 10–11)።

በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ፣ ኢየሱስ ሰውን ሊያድን እና እኛን ሊቤዠን ሰው ከሚችለው በላይ መከራን ተቀብሏል። ከእያንዳንዱ ቀዳዳ ደም ይወጣ ነበር። ንስሐ ከገባን እንዳንሰቃይ እርሱ እነዚህን ስቃዮች ስለ ሁሉ ተቀበለ (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 18፡1119፡16ይመልከቱ)።

ኢየሱስ ክርስቶስ ክህደት ደረሰበት፣ በሐሰትም ተከሰሰ፣ ተዛበቱበት እንዲሁም ገረፉት፣ የእሾህ አክሊል በራሱ ላይ ጫኑ ( ማቴዎስ 27:26፣ 29; ማርቆስ 15:15፣ 17፣ 20፣ 31; ሉቃስ 22:63; ዮሃንስ 19:1–2ይመልከቱ)። “ስለ በደላችን ደቀቀን …በእርሱ ቍስል እኛ ተፈወስን” (ኢሳይያስ 53: 5) እኛን ወደ እርሱ ለመሳብ “በመስቀል ላይ ተሰቀለ” (3 ኔፊ 27፡14–15 ይመልከቱ)። ሆኖም፣ በመስቀል ላይ እንኳን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ምህረት አደረገ (ሉቃስ 23፡34 ይመልከቱ)። ዮሐንስ እናቱን እንዲንከባከብ ጠየቀው (ዮሐንስ 19፡26–27 ይመልከዩ)። እንደተተወ ተሰማው (ማቴዎስ 27:46ማርቆስ 15:34 ይመልከቱ)። ይህም ተጠማሁ (ዮሐንስ 19፡28 ይመልከቱ) ያለው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ሁሉም ነገር ሲፈጸም፣ እርሱ በፈቃዱ “ነፍሱን ሰጠ” (ሉቃስ 23፡46፤ እንዲሁም ዮሐንስ 10፡17–18 ይመልከቱ)።

ኢየሱስ ክርስቶስ በህመማችን፣ በድካማችን፣ በብቸኝነት፣ በመገለል እና በመከራችን እንዴት እንደሚረዳን ያውቃል (አልማ 7፡12 ይመልከቱ)። እንደዚህ አይነት መከራዎች ብዙውን ጊዜ የሚመጡት በሌሎች ምርጫ መዘዝ ምክንያት ነው። በደስታችን እና በምስጋናችን ከእኛ ጋር እንዴት እንደሚደሰት፣ ደስታችን ሲሞላ እንዴት እንደሚያነባ ያውቃል። በርኅራኄ በስሙ፣ በድምፁ፣ ወደ መንጋው ይጠራናል። በሁሉም ቦታ እያንዳንዱን ሰው ይጠራል። ምድራዊ ህይወትን በዘላለማዊ እይታ እንድናይ እና እንድንረዳ ይጋብዘናል። በቅንነት ስንመላለስ እና ቃል ኪዳኖቻችንን ስንጠብቅ፣ ሁሉም ነገር በአንድነት ለጥቅማችን እንደሚሰራ ቃል ገብቷል (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 90፡24ሮሜ 8፡28 ይመልከቱ)።

በእሱ ጊዜ እና መንገድ ነገሮች ወደ ነበሩበት መመለስ ብቻ ሳይሆን መሆን ወደሚችሉበት ሊታደሱ ይችላሉ። በእውነት፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ከባርነት እና ከሃጢያት፣ ከሞት እና ከሲኦል ነጻ ሊያወጣን ይችላል፣ እንዲሁም በእምነት እና በንስሃ ከምንገምተው በላይ እንድንሆን መለኮታዊ ማንነታችንን እንድናሟላ ይረዳናል።

የመዳን ተስፋ

በኢየሱስ ክርስቶስ ምክንያት ሞት ፍጻሜ አይደለም። በትንሳኤ እኛ እንዲህ እናውጃለን-

ሞት ተሸነፈ፣ ሰው ነፃ ሆነ

ክርስቶስ ድል አድርጓል

በአባቱ ትእዛዝ እና ሃይል፣ ኢየሱስ ነፍሱን አሳልፎ መስጠት እና እንደገና ማንሳት ይችላል (ዮሐንስ 10፡17 ይመልከቱ)። በድኑ በመቃብር ውስጥ ሳለ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመንፈስ ዓለምን አደራጀ እንዲሁም “ከሞት እስራት ነፃ እንደወጡ” (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 138፡16) አገለገለ።

በሦስተኛው ቀን ጠዋት ከመቃብር ተነሳ። ማርያምን አናገራት። ወደ ኤማሁስ በሚወስደው መንገድ ላይ ለሁለት ደቀ መዛሙርት እንዲሁም ለሐዋርያቱ እና ለሌሎች ታየ። (ማቴዎስ 28ማርቆስ 16ሉቃስ 24ዮሐንስ 20⁠ን ይመልከቱ።)

በአስደናቂ ምስክርነት፣ ደቀ መዛሙርቱን መረባቸውን ከመርከቡ ማዶ እንዲጥሉ ጋበዘ፤ ምንም እንኳን መረቦቹ በዓሦች ቢሞሉም በሰአቱ አልተበጠሱም ነበር (ዮሐንስ 21፡6–11ሉቃስ 5፡3–7 ይመልከቱ)። ደቀ መዛሙርቱን መገበና ግልገሎቹን እና ጠቦቶቹን እንዲመግብ ጴጥሮስን ሦስት ጊዜ ለመነው (ዮሐንስ 21፡12–17 ይመልከቱ)። በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ፣ አሁን ደግሞ ሁላችንም የትንሳኤውን የከበረ ዜና እና ወንጌሉን ለአዝዛብ፣ ለነገድ፣ ለወገን ለቋንቋ ማካፈል እንዳለብን በማወጅ ወደ ሰማይ አረገ (ማቴዎስ 28፡19–20ማርቆስ 16፡15 ይመልከቱ)።

ኢየሱስ ክርስቶስ የኛ መልካም እረኛ እና የእግዚአብሔር በግ ነው። ነፍሱን ለበጎቹ እና ስለ በጎቹ አሳልፎ ሰጥቷል። በአትክልቱ ስፍራ እና በመስቀል ላይ ሊሸከሙት የማይቻለውን ተሸክሞ ስለኛ ሃጢያት ዋጋ ከፍሏል። በዚህች ምድር እና በዘለአለም፣ “ሞት ወደ ዘላለም የሚወስደውን መንገድ እንዴት እንደሚከፍት” በምሳሌ ያሳየናል።

በክርስቶስ የኃጢያት ክፍያ እና ትንሳኤ ሃይል አካላችን እና መንፈሳችን በአካላዊ ትንሳኤ ይገናኛሉ። ፊታችን እና ሥጋዊ ገጽታችን፣ አንዱ አካል ከሌላው ጋር ዳግም አንድ ሲሆን የከበርን እንሆናለን። የራሳችን ፀጉር እንኳን ይመለሳል። ከጊዜ፣ ከበሽታ፣ ከአካላዊ አደጋ እና ከአእምሮ ችግር ነፃ እንሆናለን። የክርስቶስ የኃጢያት ክፍያ ሁሉንም ዓይነት መንፈሳዊ መለያየትን እና መንፈሳዊ ሞትን እንድናሸንፍ ሊባርከን ይችላል። በንስሐ አማካኝነት ከእያንዳንዱ ኃጢአት እና ሀዘን ነፃ በመውጣት ወደ ዘላለማዊ የፍቅር እና የደስታ ሙላት እንደርሳለን። ንጹህ፣ ጽዱ፣ ነጻ በመሆን በጣም በምንወደው የቤተሰብ ግንኙነቶቻችን ወደ እግዚአብሄር አባታችን እና የኢየሱስ ክርስቶስ የክብር፣ ሰማያዊ መገኘት መመለስ እንችላለን።

የምንወዳቸውን ሰዎች እንደገና እናያቸዋለን። ከምንወዳቸው ጋር እንደገና ስንገናኝ፣ እርስ በርሳችን በዘለአለማዊ እይታ—በላቀ ፍቅር፣ መረዳት እና ደግነት እንተያያለን። የኢየሱስ ክርስቶስ የኃጢያት ክፍያ አስፈላጊ የሆነውን እንድናስታውስ እና የማይጠቅመንን እንድንረሳ ይረዳናል። አዳኛችንን እና ግንኙነታችንን በላቀ እምነት እና ምስጋና ማየት ሰላምን ያመጣል፣ ሸክሞችን ያነሳል፣ ልቦችን ያስታርቃል እንዲሁም ቤተሰብን በዚህ ምድር እና ለዘላለም አንድ ያደርጋል።

የዛፍ ቅርንጫፍ ከአበቦች ጋር

የመትረፍረፍ እና የደስታ ተስፋ

ትንሳኤ በኢየሱስ ክርስቶስ የሰማይ መስኮቶች መከፈትን፣ የወይኑ ፍሬ መብዛትን እና የመሬቶችን አስደሳች መሆን ያጠቃልላል። የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መበለቶችን እና ወላጅ አልባ ህፃናትን፣ የተራቡትን እና አቅመ ደካሞችን፣ የሚፈሩትን፣ የተጠቁትን ወይም ባለማወቅ በክፉ መንገድ የተያዙትን ማጽናናት እና መንከባከብን ይጨምራል። ለእያንዳንዳቸው ስለሚያስብ ልክ እንደ እርሱ በፍቅር እና በርህራሄ እንድናይ እና እንድናገለግል ኢየሱስ ክርስቶስ ይጋብዘናል።

በመልካም ነገሮች ሁሉ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በብዙ ያድሳል (ዮሐንስ 10፡10አልማ 40፡20–24 ይመልከቱ)። እርሱ “ምድር ሙሉ ናት፣ በቂ እና የሚተርፍም አለ” (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 104፡17) ሲል ቃል ገብቷል። የሁሉንም ነገር መልሶ ማቋቋሙ የወንጌሉን ሙላት፣ የክህነት ስልጣንን እና ሃይሉን፣ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ የሚገኙትን ቅዱስ ስርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች፣ በስሙ የተጠራውን የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንንም ያካትታል።

ትንሳኤ በኢየሱስ ክርስቶስ በብዙ ቦታዎች የጌታ ቤቶችን ወደ እግዚአብሔር ልጆች መቅረባቸውን ይጨምራል፣ ይህም “[በጽዮን ተራራ ላይ አዳኞች]” የሚለውን ትምህርት ወደ ልባችን ያመጣል (አብድዩ 1፡21 ይመልከቱ)። ጌታ በምድር ላይ የሞቱት ዘመዶቻቸው የሚያስፈልጋቸውን እና ለራሳቸው ማግኘት የማይችሉትን ለዘለአለም የምናቀርበውን የሚቀድስ፣ ከራስ ወዳድነት ነፃ የሆነ መንገድ አቅርቧል።

ተስፋዬ፣ ቃሌ እና ምስክርነቴ እንደዚህ ነው። ስለ እግዚአብሔር አባታችንን፤ ስለ አዳኛችን እና ቤዛችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና መንፈስ ቅዱስ እመሰክራለሁ። በትንሳኤ እንዲሁም በእያንዳንዱ ቀን፣ በእግዚአብሔር መለኮታዊ የደስታ እቅድ ውስጥ፣ ከምድራዊ ህይወት ወደ ወደ ዘላለማዊ ህይወት በሚያሸጋግረው የቃል ኪዳን መንገድ ዘላለማዊ ተስፋን እና ቃልኪድዳን እንድናገኝ እመኛለሁ። በእያንዳንዱ ቀን የኢየሱስ ክርስቶስ የኃጢያት ክፍያ እርግጠኝነት ሸክማችንን ያነሳልን፣ ሌሎችን በሀዘናቸው እንድንፅናና እና ሙሉ ደስታውን እንድንቀበል ነፍሳችንን ነፃ ያድርግልን።

በትንሳኤ ተስፋ እና ቃልኪዳን ኢየሱስ ክርስቶስ የልባችንን ናፍቆት ይሞላል እንዲሁም የነፍሳችንን ጥያቄዎች ይመልሳል።

ማስታወሻዎች

  1. ዮሐንስ 4:10፣ 146:357:37፤ በተጨማሪም ኢሳይያስ 49:10ን ይመልከቱ።

  2. ማቴዎስ 26:26–29ማርቆስ 14:22–25ሉቃስ 22:17–203 ኔፊ 18:1–11ን ይመልከቱ።

  3. He Is Risen!,” መዝሙር፣ ቁጥር 199።

  4. Upon the Cross of Calvary,”መዝሙር፣፣ ቁጥር 184።

  5. የቤተክርስቲያኗ ፕሬዚዳንቶች ትምህርቶች፡ ጆሴፍ ስሚዝ [Teachings of Presidents of the Church ] (2011)፣ 473፣ የወንጌል ላይብረሪ ይመልከቱ።