2000–2009 (እ.አ.አ)
የተበታተነውን እስራኤል መሰብሰብ
ጥቅምት 2006 (እ.አ.አ)


14:54

የተበታተነውን እስራኤል መሰብሰብ

በመጋርጃው በሁለቱም በኩል ያሉትን በጌታ የተመረጡትን ለመሰብሰብ እንረዳለን።

የተወደዳችሁ ወንደሞቼና እህቶቼ፣ ስለ እምነታችሁ፣ ስለ መሰጠታችሁ፣ እናም ስለፍቅራችሁ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ። ጌታ የሚፈልገውን አይነት ሶዎች እንድንሆን እና እሱ የሚፈልገውን እንድናደርግ አንድ ትልቅ ሃላፊነት እንጋራለን። የታላቁ እንቅስቃሴ አካል ነን—የተበታተነውን እስራኤል መሰብሰብ። በእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዕቅድ ውስጥ ልዩ ጠቀሜታ ስላለው ዛሬ ስለዚህ ትምህርት እናገራለሁ።

የአብርሃም ቃል ኪዳን

በጥንት ጊዜ ጌታ አባት አብርሃምን ትውልዱን የተመረጠ ህዝብ ለማድረግ ቃል በመግባት ባርኮታል። የዚህ ቃል ኪዳን ማጣቀሻዎች በቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ይገኛሉ። የእግዚአብሔር ልጅ በአብርሃም የዘር ሐረግ በኩል እንደሚመጣ፣ የተወሰኑ መሬቶች እንደሚወርሱ፣ የምድር አሕዛብ እና ዘሮች በእሱ ዘር እንደሚባረኩ እና ሌሎችም ተስፋዎች ተካትተዋል። የቃል ኪዳኑ አንዳንድ ገጽታዎች ቀድሞውኑ የተሟሉ ቢሆንም፣ መፅሐፈ ሞርሞን ይህ የአብርሃም ቃል ኪዳን በመጨረሻዎቹ ቀናት ብቻ እንደሚፈፀም ያስተምራል! እኛም ከጌታ ቃል ኪዳን ህዝቦች መካከል እንደሆንን አጉልቶ ያሳያል። የእኛ እድል ደግሞ እነዚህ ቃልኪዳኖች እንዲሟሉ በግል መሳተፍ ነው። ለመኖር እንዴት አስደሳች ጊዜ ነው!

እስራኤል ተበታትናለች

የአብርሃም ዘር በመሆናቸው፣ የጥንቷ እስራኤል ነገዶች የክህነት ስልጣን እና የወንጌሉ በረከቶች ነበሯቸው፣ ነገር ግን ህዝቡ ቀስ በቀስ አመጹ። እነርሱ ነብያቶችን ገደሉ እናም በጌታ ተቀጡ። አስሩ ነገዶች በአሲሪያ ውስጥ ባርነት ገቡ። ከዚያን በዉሃላ ከሰው ዘር ታሪክ መዝገብ ጠፉ። (በጌታ ፊት ግን አስሩ ነግዶች እንዳልጠፉ ግልጽ ነው።) ሁለት የቀሩት ነገዶች ለአጭር ጊዜ የቀጠሉ ሲሆን ከዚያም በማመፃቸው ምክንያት ወደ ባቢሎን ተማረኩ። ሲመለሱ በጌታ ፊት ሞገስ ነበራቸው ነገር ግን ዳግም አላከበሩትም። አልተቀበሉትም እናም ዘለፉት። አፍቃሪ ግን ሃዘን የጎዳው አባት ቃል ገባ፣ “እናንተንም ከአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፣” እናም ሁሉም ህዝብ ላይ—አደርገው።

የእስራኤል ሕዝብ እንዲሰበሰብ

ለተበተነው እስራኤል መሰብሰብ የእግዚያብሔር ቃል ኪዳን ማረጋገጫ ነበር። ለምሳሌ ኢሳያስ፣ ጌታ በኋለኛው ቀን ለነዚያ “ለሰፍሩና ለተረገጡ” ህዝቦች “ፈጣን መልእክተኞች” እንደሚልክ ተንብዮ ነበር።

በእያንዳንዱ ቅዱሳት መጻሕፍት ገጽ ላይ የተሸመነው የዚህ የመሰብሰብ ቃል ኪዳን፣ ልክ እንደ ተበተነው እስራኤል ትንቢት ይፈጸማል።

የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የዘመን መካከል እና ክህደት

ከመሰቀሉ በፊት፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያኑን አቋቋመ። ሐዋርያትን፣ ነቢያትን፣ ሰባዎቹን፣ አስተማሪዎችን እና ሌሎችንም ያጠቃልላል። ጌታም ደቀ መዛሙርቱን ወንጌልን እንዲሰብኩ ወደ ዓለም ልኳል።

በጌታ የተመሰረተችው ቤተክርስቲያን ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በመንፈሳዊ ውድቀት ወደቀች። የእርሱ ትምህርቶች ተለውጠዋል፤ ሥርዓቶቹም ተቀይረዋል። ጳውሎስ “ክህደቱ አስቀድሞ ሳይመጣ” ጌታ በድጋሚ እንደማይመጣ እንደተናገረው፣ ታላቁ ክህደት መጥቷል።

ይህ ታላቅ ክህደት እያንዳንዱን የቀደመ ዘመን ያጠናቀቀውን ንድፍ ተከትሏል። የመጀመሪያው በአዳም ዘመን ነበር። ከዚያ የሄኖክ፣ የኖህ፣ የአብርሃም፣ የሙሴ እና የሌሎች ዘመን መጣ። እያንዳንዱ ነቢይ የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን መለኮትነት እና አስተምህሮ ለማስተማር መለኮታዊ ተልእኮ ነበረው። በእያንዳንዱ ዘመን እነዚህ ትምህርቶች ሰዎችን ለመርዳት የታሰቡ ነበሩ። አለመታዘዛቸው ግን ክህደትን አስከተለ። ስለሆነም፣ ሁሉም የቀደሙት ዘመናት በጊዜ እና በቦታ ተወስነዋል። እያንዳንዳቸው በክህደት ስለተጠናቀቁ በጊዜ ተገድበው ነበር። እነሱ በመጠኑ አነስተኛ በሆነ የፕላኔቷ ምድር ክፍል ውስጥ በቦታ ተወስነው ነበር።

የሁሉም ነገሮች በዳግም መመለስ

ስለሆነም የተሟላ ተሃድሶ ያስፈልግ ነበር። እግዚአብሔር አብ እና ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የዚህ ዘመን ነቢይ እንዲሆን ጠርተውታል። የቀደሙት ጊዜያት መለኮታዊ ኃይሎች ሁሉ በእርሱ አማካይነት ሊመለሱ ነበር። የዘመናት ሙሉነቱ በጊዜ ወይም በቦታ አይገደብም። በክህደት አይጠናቀቅም አናም ዓለምን ይሞላል።

የእስራኤል መሰብሰቢያ—የሁሉም ነገሮች እድሳት አንድ አካል ነው።

በጴጥሮስና በጳውሎስ እንደተነበየው፣ በዚህ ዘመን ሁሉም ነገሮች እንደገና ወደነበሩበት መመለስ ነበረባቸው። ስለዚህ፣ የዳግም መመለስ አካል ሆኖ ከረጅም ጊዜ በፊት ሲጠበቅ የኖረው የተበታተነው የእስራኤል መሰብሰብ መምጣት አለበት። ለጌታ ዳግም ምጽዓት አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት ነው።

ይሄ የመሰብሰብ ትምህርት በኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አስፈላጊ ከሆኑ ትምህርቶች አንዱ ነው። “ህዝቤን የእስራኤልን ቤት፣ ለረጅም ጊዜ ከተበተኑበት የምሰበስብበት፣ እናም በድጋሚም ፅዮንንም በመካከላቸው የምመሰርትበት የሚፈፀሙበትን ጊዜ ታውቁ ዘንድ ምልክትን እሰጣችኋለሁ” በማለት ጌታ አውጇል። የመፅሐፈ ሞርሞን መምጣት ጌታ እስራኤልን ለመሰብሰብ እና ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ እና ለያዕቆብ የገባላቸውን ቃልኪዳን ለመፈፀም መጀመሩን ለዓለም ሁሉ ምልክት ነው። እኛ ይህንን ትምህርት ማስተማር ብቻ ሳይሆን ተሳትፎም እናደርጋልን። በመጋረጃው በሁለቱም በኩል ያሉትን በጌታ የተመረጡትን ለመሰብሰብ እንረዳለን።

መፅሐፈ ሞርሞንም ለዚህ ስራ ማዕከላዊ ክፍል ነው። የስብሰባውን አስተምህሮ ያውጃል ሰዎች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲማሩ፣ በወንጌሉ እንዲያምኑ እና ወደ ቤተክርስቲያኑ እንዲቀላቀሉ ያደርጋቸዋል። በእርግጥም፣ መጽሐፈ ሞርሞን ባይኖር ኖሮ፣ ቃል የተገባው የእስራኤል መሰባሰብ አይከናወንም ነበር።”

ለእኛ ግን የተከበረው የአብርሃም ስም አስፈላጊ ነው። ከአጠቃላይ መጽሃፍ ቅዱስ ካሉ ጥቅሶች ይልቅ ዳግም በተመለሱት ቅዱሳን መጻህፍቶች ውስጥ ተጠቅሷል። አብርሃም ከሁሉም የኋለኛው ቀን ቅዱሳን ቤተክርስቲያን አባላቶች ጋር የተቆራኘ ነው። ጌታ የአብርሃማዊውን ቃል ኪዳን በነብዩ ጆሴፍ ስሚዝ በኩል አረጋግጧል። በቤተመቅደስ ውስጥ እንደ አብርሃም፣ የይስሐቅ እና የያዕቆብ ዘር ዋና በረከቶቻችንን እንቀበላለን።

የጊዜያት ሙሉነት ዘመን

ይህ የዘመን ሙላት ዘመን በሰማይ እና በምድር መሰብሰቢያ ጊዜ በእግዚአብሔር አስቀድሞ ታወቀ። ጴጥሮስ ከተወሰነ የክህደት ጊዜ በኋላ ዳግም መመለስ እንደሚመጣ ያውቅ ነበር። በመለወጫ ተራራ ከጌታ ጋር የነበረው፣ እሱ ተናገረ፤

“እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም፤ …

“እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው፥ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።”

በአዲሱ ዘመን ሐዋርያቱ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ እና ዮሐንስ “ለእነርሱም በሰማይ እና በምድር ያሉትን ነገሮች ሁሉ በአንድ በምጠቀልልበት በዘመናት ሙላት፣ የዚህን የዘመነ ፍጻሜን ወንጌልንና የመንግስቴን ቁልፎች ለመጨረሻው ጊዜ ከሰጠኋቸው” ጋር፤ በጌታ ተልከው ነበር።

በ1830 (እ.አ.አ)፣ ነብዩ ጆሴፍ ስሚዝ ኤልያስ የተባለ “የሁሉም ነገሮች ዳግም መመለስ” ቁልፍ የያዘ የሰማይ መልእክተኛ አወቀ።

ከስድስት ዓመታት በኋላ የከርትላንድ ቤተመቅደስ ተመረቀ። ጌታ ያንን ቅዱስ ቤት ከተቀበለ በኋላ፣ የሰማይ መልእክተኞች የክህነት ቁልፎችን ይዘው መጡ። እና ሙሴ በፊታችን መጣ፣ እና ከምድር አራት ማዕዘናትን የእስራኤልን መሰብሰቢያ እና ከሰሜን ምድር የአስሩን ነገዶች መምሪያ ቁልፎችን ሰጠን።

ከዚህ በኋላ፣ ኤልያ መጣ፣ እና በእኛና በዘራችን ከእኛም በኋላ የሚመጡ ትውልዶች ሁሉ ይባረካሉ በማለት የአብርሐም ወንጌል የዘመን ፍጻሜን ሰጠን።”

ነብዩ ኤልያስ መጥቶ እንዳወጀው፣ “እነሆ፣ በሚልክያስ አንደበት በመመስከር ተነግሮ የነበረው ጊዜ በሙላት መጥቷል—ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ እርሱ [ኤልያስ] እንደሚላክ—ይህም፣ ምድር በእርግማን እንዳትመታ፣ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች፥ የልጆችንም ልብ ወደ አባቶች ለመመለስ እንዳለበት ተነግሮ የነበረው ጊዜ በሙላት መጥቷል።”

የሚልኪያስ ትንቢት ይፈጸም ዘንድ፣ እነዚህ ክስተቶች በሚያዝያ 3 ቀን 1836 (እ.አ.አ.) ተከሰቱ። የዚህ ዘመን ቅዱሳን ቁልፎች ተመልሰዋል።

በመጋረጃው ሌላኛው ክፍል የነፍሳት መሰባሰብ

“ወደ ክርስቶስ እንድትመጡ” የሚለው ግብዣ፣ ስለወንጌሉ ሳያውቁ ለሞቱት በምህረት ሊዘረጋ ይችላል። የዝግጅታቸው አካል የሌሎችን ምድራዊ ጥረቶች ይጠይቃል። የዘር ሐረጎችን ሰበሰብን፣ የቤተሰብ ቡድን ወረቀትን ፈጠርን፣ እና ግለሰቦችን ወደ ጌታ እና ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመሰብሰብ የቤተመቅደስን ሥራ በጥልቀት ሰራን።

በስብሰባው ላይ ለመሳተፍ፤ በቃል ኪዳን ዓላማ መጽናት

በዚህ ምድር ላይ፣ የሚሲዮናዊ ስራ ለእስራኤል መሰብሰብ ወሳኝ ነው። ወንጌሉ በመጀመሪያ ሊወሰድ የነበርው “የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች” ነበር። በዚህ ምክንያት፣ የጌታ አገልጋዮች ዳግም መመለስን ለማወጅ ወጥተዋል። በብዙ አገሮች ውስጥ ሚስዮናዊያኖቻችን የተበታተኑትን እስራኤል ፈልገዋል፤ “ከየድንጋዩም ስንጣቂ ውስጥ” አድነዋቸዋል፣ እንደ ጥንቱ ጊዜም እነርሱን አጥምደዋቸዋል።

ወደ ክርስቶስ የመምጣታችሁ ምርጫ በቦታ የሚወሰን አይደልም፤ የግል ቁርጠኝነት ጉዳይ ነው። ሰዎች የትውልድ አገራቸውን ሳይለቁ “አዳኛቸው ወደ ሆነው ወደ ጌታ አምላካቸው እውቀት ይመጣሉ።” እውነት ነው፣ በቤተክርስቲያኗ የመጀመሪያ አመታት፣ ብዙውን ጊዜ መለወጥ መሰደድ ማለት ነበር። አሁን ግን መሰብሰቡ የሚከናወነው በእያንዳንዱ አገር ውስጥ ነው። ጌታ ለቅዱሳኑ ልደታቸውን እና ዜግነታቸውን በሰጣቸው በእያንዳንዱ ግዛት ጽዮን እንድትመሰረት ወስኗል። ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚናገሩት “ሰዎች ወደ ርስታቸው ሀገሮች ይሰበሰባሉ፣ በተስፋቸውም ምድሮች ሁሉ ይቋቋማሉ።” “የሰው ዘር በሙሉ ለራሱ ህዝብ መሰብሰቢያ ነው።” ለብራዚል ቅዱሳን የተሰበሰቡበት ቦታ በብራዚል ነው፤ ለናይጄሪያ ቅዱሳን መሰብሰቢያ ቦታ ናይጄሪያ ውስጥ ነው፤ የኮሪያ ቅዱሳን መሰብሰቢያ ቦታ በኮሪያ ውስጥ ነው፤ ወዘተ። ፅዮን “ልበ ንጹህ” ናት። ጺዮን ቅዱስ ጻድቃን ባሉባት ቦታዎች ሁሉ ናት። ሁሉም አባላት ህትመቶችን፣ ግንኙነቶች እና ጉባኤዎችን አሁን የወንጌልን ትምህርቶችን፣ ቁልፎችን፣ ስርአቶች እና በረከቶችን ከየትም ቦታ ሆነው ማግኘት ይችላሉ።

መንፈሳዊ ደህንነት ሁል ጊዜ የሚወሰነው እንድ ሰው እንዴት እንደሚኖር እንጂ፣ የሚኖርበት ቦታ አይደለም። በሁሉም ምድር ያሉ ቅዱሳን በጌታ በረከቶች ላይ እኩል መብት አላቸው።

ይህ የልዑል እግዚአብሔር ሥራ እውነት ነው። እርሱ ህያው ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ቃል የተገባውን የእስራኤልን መሰብሰብ ጨምሮ መለኮታዊ ዕጣዋን ለመፈፀም የተመለሰችው ይህች ቤተክርስቲያን ናት። ፕሬዘዳንት ጎርደን ቢ. ሂንክሊይ ዛሬ የእግዚአብሔር ነቢይ ናቸው። ስለዚህ የምመሰክረው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው፣ አሜን።

  1. ዘፍጥረት 12፥1-2ት&እና ቃ 132፥29-32አብርሃም 2፥6-11ይመልከቱ።

  2. ዘፍጥረት 26፥1–4, 24, 2835፥9–1348፥3–4; ዮሃንስ 8፥33, 39የሃዋርያት ስራ 3፥251 ኔፊ 17፥402 ኔፊ 29፥14ያቆብ 5አስቴር 13፥7–8ት&እና ቃ 52፥2ይመልከቱ።

  3. ለምሳሌ 1 ኔፊi 15:12–18

  4. 1 ኔፊ 14፥1415፥142 ኔፊ 30፥2ሞዛያ 24፥133 ኔፊ 29፥3ሞርሞን 8፥15ት&እና ቃ 133፥26-34 ይመልከቱ

  5. የሌዊ ነገድ በሕዝቡ መካከል ካህናትን ያቀረበ ሲሆን እንደ ነገድ ተቆጥሮ ወይም የጎሳ ውርስ አይቀበልም ነበር። ሁለቱ የዮሴፍ ልጆች፣ ምናሴ እና ኤፍሬም፣ የመሬት ውርስ ተሰጣቸው። በአባታቸው በዮሴፍ ምትክ፣ ከነገድ መካከል ተቆጠሩ። የአሥራ ሁለት ነገዶች ቁጥር እንዲሁ ተጠብቆ ነበር።

  6. ዘሌዋውያን 26፥33ኤርሚያስ 9፥16፣ ተመልከቱ።

  7. ዘፍጥረት 12፥-18-23ኛ ኔፊ 20-22አብርሃም 2፥10-11ተመልከቱ።

  8. ኢሳያስ 18፥2-7

  9. ዘሌዋውያን 26፥44ዘዳግም 4፥27-31282930፥205ነህምያ 1፥9ኢሳያስ 11፥11-12ኤርሚያስ 31፥7-8 10-12ሕዝቅኤል 37፥21-22አሞጽ 9፥14-15ማቴዮስ 24፥31ያዕቆብ 6፥2፤ Russell M. Nelson, “The Exodus Repeated,” Liahona, ሚያዝያ 2002 እ.አኤ.አ 30-39 እንዛይንሃምሌ 1999 እ.ኤ.አ 6-13

  10. ሉቃስ 10፥1 17ኤፌሶን 4፥11የእምነት አንቀጽ 1፥6ይመልከቱ።

  11. ማቴዎስ 28፥19–20ማርቆስ 15፥27–28ይመልከቱ።

  12. 2 ተሰሎንቄ 2፥3። “መውደቅ” የሚለው የተተረጎመው፣ ከግሪክ ቃል ሲሆን አፖስታሲያትርጓሜው “ክህደት”።

  13. ት&እና ቅ 128፥18132፥45ይመልከቱ።

  14. ኢሳይያስ 27፥6ይመልከቱ።

  15. 1ኛ ኔፊ 15፥18፤ ይመልከቱ የመፅሐፈ ሞርሞን ርዕስ ገጽ፣ አንቀጽ 2

  16. ት&እና ቃ 133፥17ይመልከቱ።

  17. 3ኛ ኔፊ 21፥1

  18. ዘፍጥረት 12፥2-326፥3-435፥11-123 ኔፊ 2129

  19. የእስራኤል ቤት መበታተን እና መሰባሰብን የሚመለከቱ ትምህርቶች በመፅሐፈ ሞርሞን ውስጥ ከተሰጡት ቀደምት ትምህርቶች መካከል፤ “እናም የእስራኤል ቤቶች ከተበተኑ በኋላ እንደገና በአንድ ላይ መሰብሰብ አለባቸው፤ … የወይራው ዛፍ ተፈጥሮአዊ ቅርንጫፎች፣ ወይም በአጠቃላይ የእስራኤል ቤት ቅሪት ይጣበቃሉ፣ ወይም የእነርሱ መድሐኒትና ጌታ ወደሆነው እውነተኛ መሲሕ እውቀት ይመጣሉ” (1ኛ ኔፊ 10፥14)ይመልከቱ።

  20. ብሩስ አር. ማኮንኪ፣ ለእምነት አንቀጾች አዲሱ ምስክር (1985)፣ 554 ተመልክቱ።

  21. አብርሃም በ 506 የቅዱሳት መጻሕፍት ቁጥሮች ውስጥ ተጠቅሷል፥ 216 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛሉ፤ 290 በዳግም መመለስ መጻሕፍት ውስጥ ናቸው።

  22. ቃል ኪዳኑንም በፍቃደኝነት መቀበል ይቻላል።( ማቲዮስ 3፥9ሉቃስ 3፥8ገላቲያ 3፥26–294፥5–7አብርሃም 2፥9-10) ተመልከቱ።

  23. ት&እና ቃ 124፥58132፥31-32 ተመልከቱ።

  24. ት&እና ቃ 84:33–40; 132፥19አብርሃም 2፥11ይመልከቱ።

  25. ስራ 3፥19 21

  26. ት&እና ቃ 27፥13። በተጨማሪም ጳውሎስ ስለ ዘመናችን ተንብዮአል “በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው” (ኤሬሶን 1፥10)።

  27. ት&እና ቃ 27፥6.

  28. መጀመሪያ የእግዚአብሔርን ልጆች ወደ ርስታቸው ምድር የመራቸው ሙሴ፣ የእስራኤልን መሰብሰብ ቁልፎች ለተመለሰችው ቤተክርስቲያን መስጠቱ ተገቢ ነው። ሙሴ ወደ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ እና ዮሐንስ በተለወጠው ተራራ ላይ መጥቶ በዘመናቸው ተመሳሳይ የክህነት ቁልፎችን ሰጣቸው። ነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በሚያዝያ 1840 (እ.አ.አ)፣ በቤተክርስቲያኗ ጉባኤ ኦርሰን ሃይዴን ወደ ኢየሩሳሌም እንዲሄድ ሾመው እና እዚያም አይሁዶች እና ለተበተኑ እስራኤል ምድርን እንዲወስኑ አደረገ። እሁድ ጥቅምት 24 ቀን 1841(እ.አ.አ)፣ ሽማግሌው ሃይዴ በደብረ ዘይት ተራራ ተንበርክኮ አይሁድን እና እስራኤልን ወደ ጥንታዊ ውርሳቸው ለመሰብሰብ ያንን መሬት ወሰነ።

  29. ት&እና ቃ 110፥ 11–2

  30. ት&እና ቃ 110፥ 14– 15

  31. ሙሴ፣ ኤልያስ እና ኤልያስ በፋሲካ እሑድ በማለፍ በአል መጀመሪያ ላይ የመጡት እውነታ አስፈላጊ ነው።

  32. ሚልክያ 4፥5–6ይመልከቱ።

  33. ት&እና ቃ 110፥16ይመልከቱ።

  34. ያቆብ 1፥7ኦምኒ 1፥26ሞሮኒ 10፥30-32ት&እና ቃ 20፥59ይመልከቱ።

  35. ት&እና ቃ 137:6–8ይመልከቱ።

  36. 1ኛ ቆሮንጦስ 1፥28–291 ጴጥሮስ 4፥6ይመልከቱ።

  37. ማቴዎስ 10፥615፥24.

  38. ኤርሚያስ 16፥16ይመልከቱ።

  39. 3ኛ ኔፊ 20፥13

  40. ት&እና ቃ 6፥611፥612፥614፥6ይመልከቱ።

  41. 2 ኔፊ 9፥2

  42. ብሩስ አር መካንኬ፣ በጉባኤ ሪፖርት፣ ሜክሲኮ ሲቲ ሜክሲኮ የአካባቢ ጉባኤ 1972 (እ.አ.አ)፣ 45።

  43. ት&እና ቃ 97፥21.