“የአይሁድ ፋሲካ፣” ጓደኛ፣ ሚያዝያ 2026 (እ.አ.አ)፣ 46–48።
ወርሐዊ የጓደኛ መልእክት፣ ሚያዝያ 20216 (እ.አ.አ)
የአይሁድ ፋሲካ
ሙሴ ወደ ፈርዖን ሄደ እና የእስራኤላውያን ባሮችን ነሻነት እንዲሰጣቸው ጠየቀው። ፈርዖን እምቢ አለ። ጌታ ወደ ግብጽ መቅሰፍት ላከ፣ ፈርዖኑ አሁንም እምቢ አለ።
ጌታ አንድ የመጨረሻ መቅሰፍት እልካለሁ አለ። የእያንዳንዱ ግብጻዊ ቤተሰብ የበኩር ልጅ ይሞታል። እስራኤላውያን የእርሱን መመሪያዎች ከተከተሉ መቅሰፍቱ ከእነርሱ እንደሚያልፍ እና እንደማይጎዳቸው ጌታ ቃል ገባ።
ጌታ እያንዳንዱ የእስራኤል ቤተሰብ እንከን የለሽ ወንድ ጠቦት መሥዋዕት በማድረግ የጠቦቱን ደም በቤታቸው በር ላይ እንዲቀቡ ነገራቸው።
መቅሰፍቱ መጣ። የፈርዖን ወንድ ልጅን ጨምሮ፣ ሁሉም የግብጻውያን የበኩር ልጆች ሞቱ። ለጌታ ታዛዥ በመሆናቸው ምክንያት የእስራኤላውያን የበኩር ልጆች ዳኑ።
ፈርዖኑ ሙሴ እና እስራኤላውያን ከግብፅ እንዲወጡ ነገራቸው። ግን ፈርዖኑ ተናድዶ ነበር። እርሱ እና ሰራዊቱ እነርሱን አሳደዱ።
እስራኤላውያን በቀይ ባህር አጠገብ ሰፈሩ። እስራኤላውያን ግብፃውያን ሲመጡ ባዩ ጊዜ ፈርተው ነበር። ሙሴም ጌታ ይጠብቃቸዋል አለ።
ሙሴም በትሩን ከፍ አደረገ፣ እናም ጌታ ባህሩን ከፈለው። እስራኤላውያን ባሕሩን በደረቅ መሬት ተሻገሩት።
እስራኤላውያን ሁሉ በባሕሩ ማዶ በደህና ሲደርሱ፣ ውኃው ተመልሶ የግብጽ ሠራዊትን አሰጠመ። እስራኤላውያን በስተመጨረሻ ነጻ ሆኑ።
የሚቀባ ገፅ
ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኔ ከሞት ተነስቷል
ስዕል በኦድሪ ደይ። ለቤተክርስቲያኗ ጥቅም ብቻ መባዛት ይቻላል።
በዚህ ፋሲካ እና በአመት በሙሉ ኢየሱስ ክርስቶስን ለማስታወስ ምን ማድረግ ትችላላችሁ?
© 2026 by Intellectual Reserve, Inc. All rights reserved. በዩ.ኤስ.ኤ የታተመ። እንግሊዘኛ የተፈቀደበት፦ 6/19። ትርጉም የተፈቀደበት፦ 6/19። Monthly Friend Message, April 2026 ትርጉም። Amharic. 20062 506