”ኖህ እና መርከቡ፣” ጓደኛ፣ የካቲት 2026፣ 46-48።
ወርሃዊ የ ጓደኛ መልእክት፣ የካቲት 2026 (እ.አ.አ)
ኖኅ እና መርከቡ
ኖኅ እና ቤተሰቡ ጌታን ታዘዙ። ሁሉም ሌሎች ሰዎች በጣም ኃጢያተኞች ነበሩ። ህዝቡ ንስሃ ካልገቡ ጌታ በጥፋት ውኃ ምድርን እንደሚሸፍን ለኖኅ ነገረው።
ኖኅ ጌታ እንደወደዳቸው እንዲሁም ንስሐ እንዲገቡ እና በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እምነት እንዲኖራቸው እንደሚፈልግ ህዝብን አስተማረ። እነርሱም አላደመጡም።
ጌታ ቅስት የተባለውን ትልቅ መርከብ እንዲሠራ ነገረው። መርከቡ በጥፋት ውኃው ወቅት የኖኅን ቤተሰብ ደህንነት ይጠብቃል።
የኖኅ ቤተሰብ ምግብ ወደ መርከቡ አመጡ። ጌታ ቢያንስ ከእያንዳንዱ እንስሳት አይነቶች ሁለት ሁለቱን ወደ ኖኅ ላከ። ከዚያም መዝነብ ጀመረ።
ለ40 ቀናት እና 40 ሌሊት ያህል ዘነበ። ልክ ጌታ እንዳስጠነቀቀው፣ ጎርፍም ምድርን ሸፈናት።
የኖኅ ቤተሰብ እና በመርከቡ ውስጥ ያሉት ሁሉም እንስሳት በደህና በውኃው ላይ ተንሳፈፉ።
የጥፋት ውኃው ሲያልቅም የኖኅ መርከብ በደረቅ መሬት ላይ አረፈች። ኖኅ እና ቤተሰቡ ስለጠበቃቸው ጌታን አመሰገኑ። ጌታ ምድርን ዳግመኛ በጥፋት ውኃ በፍጹም እንደማያጥለቀልቅ ቃል ገባ። የገባውን ቃል ለማስታወስ ቀስተ ደመናን ላከ።
የሚቀባ ገፅ
የጌታን ነብይ መከተል ይባርከኛል።
ገለጻ በኦድሪ ዴይ
ነቢዩን ለመከተል ምን ማድረግ ትችላላችሁ?
© 2026 by Intellectual Reserve, Inc. መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው። በዩ.ኤስ.ኤ ውስጥ ታተመ። እንግሊዘኛ የተፈቀደበት፦ 6/19። ትርጉም የተፈቀደበት፤ 6/19። Monthly Friend Message, February 2026ትርጉም። Amharic. 19927 506