ጓደኛ
አዳም እና ሔዋን
ጥር 2026 (እ.አ.አ) ጓደኛ


“አዳም እና ሔዋን፣” ጓደኛ፣፣ ጥር 2026 (እ.አ.አ)፣ 46–48።

ወርሃዊ የ ጓደኛ መልእክቶች፣ ጥር 2026 (እ.አ.አ)

አዳም እና ሔዋን

አዳምና ሔዋን በኤደን ገነት ከእንስሳት ጋር

አዳም እና ሔዋን በምድር ከኖሩት የእግዚአብሔር ልጆች መካከል የመጀመሪያዎቹ ነበሩ። በኤደን ገነት ውስጥ ይኖሩ ነበር።

የህይወት ዛፍ

ከአንዱ በስተቀር ከሁሉም የዛፍ ፍሬ እዲበሉ እግዚአብሔር ፈቀደላቸው። መልካምንና ክፉን ከሚያሳውቀው ዛፍ ከበሉ፣ ከገነት መውጣት አለባቸው እንዲሁም በመጨረሻም ይሞታሉ። ሰይጣን ግን ዋሻቸው። ሰይጣን፣ ፍሬውን ከበሉ መልካምን እና ክፉን ያውቃሉ እንጂ አይሞቱም አለ።

ሔዋን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ ፍሬ እየወሰደች።

ሔዋን ፍሬውን ለመብላት መረጠች።

የሔዋን እጆች ፍሬውን ወደ አዳም እጅ ሲያስተላልፉ

ሔዋን ለአዳም ከፍሬው ጥቂቱን ሰጠችው። እርሱም ሊበላው መረጠ።

አዳምና ሔዋን የሰማይ አባት እና ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጡ በቁጥቋጦ ውስጥ ሲደበቁ

እግዚአብሔር እና ኢየሱስ ክርስቶስ ጎበኙዋቸው፣ ነገር ግን አዳም እና ሔዋን ፈርተው ነበር እናም ተደበቁ። እግዚአብሔር ከዛፉ ፍሬ በልተው እንደሆነ ጠየቀ።

አዳምና ሔዋን የቆዳ ልብስ ለብሰው ከኤደን ገነት ሲወጡ

አዳምና ሔዋን ፍሬውን በልተናል አሉ። አሁን ከኤደን ገነት መውጣት ይኖርባቸዋል። እግዚአብሔር ግን ለእነርሱ እቅድ ነበረው። አሁን መልካምን ከክፉ አውቀው ነበር እንዲሁም ልጆችን መውለድ ቻሉ።

አዳም እና ሔዋን ከቤተሳቦቻቸው ጋር

አዳም እና ሔዋን የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት በሙሉ ለማክበር ቃል ገቡ። ስለ እግዚአብሔር ልጅ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የበለጠ ተማሩ። ቤተሰባቸውን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ እርሱ ሊረዳቸው ስለሚችል ደስተኞች ነበሩ።

ቀለም የሚቀባ ገፅ

ኢየሱስ ምድርን ፈጠረ።

የፒዲኤፍ ገጽ

በኦድሪ ዴይ የተሳለ ስዕል

ኢየሱስ ክርስቶስ ከፈጠራቸው ነገሮች ውስጥ ምትወዱት የትኞቹ ናቸው?