“ቅዱሳን ወደ ምዐዕራብ ይሄዳሉ፣” ጓደኛ፣ ታህሳስ 2025፣ 26-28።
ወርሃዊ የ ጓደኛ መልእክት፣ ታህሳስ 2025 (እ.አ.አ)
ቅዱሳን ወደ ምእራብ ይሄዳሉ
ጆሴፍ ስሚዝ ከሞተ በኋላ፣ ብሪገም ያንግ እና ሌሎች ሃዋርያት ቤተክርስቲያኒቱን መርተዋል። ሁኔታው አመቺ ስላልነበር ቅዱሳን ናቩን ለቀው መሄድ እንደነበረባቸው ብሪግሃም ያንግ አውቀዋል። ነገር ግን በመጀመሪያ፣ ጌታ የቤተመቅደሱን ግንባታ እንዲያጠናቅቁ ፈልጓል።
ቤተመቅደሱም ዝግጁ በሆነ ጊዜ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ቅዱሳን ከጌታ ጋር ቃልኪዳንን አደረጉ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተጣምረዋል።
አሁን ወደ ምእራብ ጉዟቸውን የሚጀምሩበት ወቅት ነበር። የአየሩ ሁኔታ ቀዝቃዛ ነበር፣ ህዝቡም ታመው እና ተርበው ነበር።
ብሪገም እርዳታ ለማግኘት ጸለዩ። ጌታ እርስ በርስ መረዳዳት እንዳለባቸው እና እርሱም እንደሚባርካቸው እና እንደሚረዳቸው ተናገረ።
አሁንም ጉዞው በጣም ከባድ ነበር። አንዳንድ ሰዎችም ሞቱ። ነገር ግን በቤተመቅደሱ ቃል ኪዳናቸው ምክንያት፣ ቅዱሳን የቤተሰብ አባሎቻችውን ዳግም እንደሚያገኟቸው አውቀዋል።
የመጀመሪያዎቹ ቅዱሳን በ1847 (እ.አ.አ) ወደሶልት ሌክ ሸለቆ ደርሰዋል። በዚህ ጌታን ሊያመልኩት እና ስራውንም በሰላም ሊሰሩ ይችላሉ።
በዓመታት መካከል፣ ብዙ ቅዱሳን ወደዚህ ደርሰዋል እናም ብዙ ቤተመቅደሶችንም ገንብተዋል። የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ለማስተማር በዓለም ዙሪያ ሚስዮናውያንን ተጉዘዋል። በየስፍራው የሰማይ አባት ልጆችን እየባረከች፣ የአዳኙ ቤተክርስቲያን ማደጓን ቀጥላለች።
የሚቀባ ገፅ
እርሱ የአለም ብርሀን፣ ህይወት እና ተስፋ ነው።
ስዕል በኮሪ ኤግበርት
በገና ወቅት ኢየሱስ ክርስቶስን ለማስታወስ ምን ታደርጋላችሁ?
© 2025 by Intellectual Reserve, Inc. መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው። በዩ.ኤስ.ኤ ውስጥ ታተመ። እንግሊዘኛ የተፈቀደበት፦ 6/19። ትርጉም የተፈቀደበት፤ 6/19። Monthly Friend Message, December 2025 ትርጉም። Amharic. 19637 506