ወርሃዊ የ ጓደኛ መልእክት፣ ሐምሌ 2025 (እ.አ.አ)
ሐዋርያት በታላቋ ብሪታንያ ሚስዮን አገለገሉ
ጌታ አንዳንድ ሐዋርያትን ለሚስዮን ወደ ታላቋ ብሪታንያ እንዲልክ ለጆሴፍ ስሚዝ ነገረው። ቤተሰቦቻቸውን ትተው መሄድ ለሐዋርያትም ከባድ ነበር፣ ነገር ግን ጌታ ሊባርካቸው ቃል ገብቶላቸዋል።
ሒበር ሲ. ኪምባል እና ሚስቱ ቪላቴ ታዳጊ ቤተሰብ ነበራቸው። ከእነርሱም ብዙዎቹ ታመው ነበር።
ብሪገም ያንግም እንዲሁ ታምሞ ነበር፣ እና ቤተሰቡም ድሃ ነበር። ነገር ግን የብሪገም ሚስት፣ ሜሪ አን፣ “ሂድ እና በሚስዮን አገልግል፣ ጌታም ይባርክሃል” አለችው።
ሒበር እና ብሪግሃም ተሽሏቸው ነበር፣ ሆኖም በጣም አቅም አንሷቸው ነበር። ወንጌልን ለመስበክ ፈልገዋል፣ በመሆኑም ቤተሰቦቻቸውን ተሰናበቱ እናም ጉዞአቸውንም ለመጀመር በአንድ ሰረገላ ኋላ ወጡ።
ከውቅያኖሱ ባሻገር ረጅም ጉዞ ካደረጉ በኋላ፣ ሒበር እና ብሪግሃም ወደ ታላቋ ብሪታንያ ደረሱ። ከሌሎች ሐዋርያት ጋር፣ አያሌ ሰዎችን ወንጌል አስተማሩ። በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአዳኙ ቤተክርስቲያን ተጠምቀዋል። ከእነርሱም አብዛኞቹ በዩናይትድ ስቴትስ የነበሩ ቅዱሳንን ለመቀላቀል ከውቂያኖስ ባሻገር ተጉዘዋል።
እነርሱ በሚስዮናዊ አገልግሎት ላይ ሳሉ ጌታ የሒበርን እና የብሪግሃምን ቤተሰብ እንደሚንከባከባቸው የገባውን ቃል ጠበቀ።
የሚቀባ ገፅ
እግዚአብሔር በምድር ላይ ያለውን ፍጥረት ሁሉ ፈጠረ።
ምስል በኮሪ ኢግበርት
የምትወዱት ፍጥረት ምንድነው?
© 2025 by Intellectual Reserve, Inc. መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው። በዩ.ኤስ.ኤ ውስጥ የታተመ። እንግሊዘኛ የተፈቀደበት፦ 6/19። ትርጉም የተፈቀደበት፤ 6/19። Monthly Friend Message, July 2025. ትርጉም። Amharic. 19639 506